በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለሥልጣን መ/ቤት በ2018 በጀት አመት ከካፒታል በጀት ለመ/ቤቱ የተለያዩ ተሽከርካሪዎችና ማሽነሪዎች አገልግሎት የሚውል መለዋወጫ (ስፔር ፓርት) በሎት 1/አንድ እንዲሁም ጎማና ባትሪ በሎት 2/ሁለት/ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለሥልጣን መ/ቤት በ2018 በጀት አመት ከካፒታል በጀት ለመ/ቤቱ የተለያዩ ተሽከርካሪዎችና ማሽነሪዎች አገልግሎት የሚውል መለዋወጫ (ስፔር ፓርት) በሎት 1/አንድ እንዲሁም ጎማና ባትሪ በሎት 2/ሁለት/ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት የምትችሉ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
- በዘመኑና በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ሥራ ፈቃድ ያለው።
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN NO) ያላቸው እና የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸው የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል ።
- በጨረታ ለመሳተፍ የሚያገለግል ከገቢዎች የተጻፈ ማስረጃ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል።
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር ከ1-2 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
- ጨረታው ጸንቶ የሚቆይበት ጊዜ የጨረታ ሰነዱ ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ለ60 ቀናት ሲሆን ተጫራቶች የጨረታ ማስከበሪ ዋስትና (BID BOND) ብር የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ 2% በማስላት ለእያንዳንዱ ሎት በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣያ (CPO) በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ ማቅረብ አለበት፡፡
- ማንኛውም ተጫራች መ/ቤቱ ባዘጋጀው የጨረታ ሰነድ በሚጠይቀው የዋጋ አሞላል ብቻ መሙላት አለበት። በሚጠይቀው ዋጋ አሞላል ካልሞሉ የጨረታ ሰነዱ ውድቅ ይሆናል ፡፡
- የጨረታው ውድድር የሚካሄደው በእያንዳንዱ ሎት /በጥቅል/ ድምር ውጤት ስለሆነ የማይሞላ አይተም መኖር የለበትም ያልተሞላ አይተም ከተገኘ ከጨረታው ውድቅ ይሆናሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኪሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል ከግ/ፋይ/ን/አስ/ደ/የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 508 ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው አየር ላይ የሚቆየው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከ14/02/2018 ዓ.ም እስከ 28/02/2018 ዓ.ም 11፡30 ድረስ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆነ አንድ ቅጅ ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት ለየብቻ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ መንገዶች ባለሥልጣን መ/ቤት በግዥና/ፋይ/ን/አስ/ደ/የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 508 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት እስከ 29/02/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥና ፋይ/ን/አስ/ደ/የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 508 29/02/2018 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በ 4፡30 ላይ ይከፈታል ነገር ግን ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ቅዳሜ ፣እሁድ የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይንም በከፈል የመሰርዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ለበለጠ መረጃ በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለሥልጣን መ/ቤት በአካል በመቅረብ ወይንም በስልክ ቁጥር 033 35 33 37/033 551 05 04/ መጠየቅ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
ማሳሰቢያ፡- ሁሉም ተጫራቾች በተጫራቾች መመሪያ መሰረት የማጭበርበር ድርጊት ላለመፈጸም ቃል የሚገቡበትን ቅጽ ፈርሞ የድርጅቱን ማህተም በመምታት ጨረታ ሰነዱ ጋር ማስገባት አለበት፡፡ የመስሪያ ቤቱ አድራሻ ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ህንጻ አምስተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 508 ላይ ነው።
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን
