በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የትምህርት ቢሮ አገልግሎት የሚውል የልብስ ስፌት ማሽን ግዥ ከዚህ በታች በቀረበው መሰረት ግዥ ለመከናወን ሕጋዊ ድርጅቶችን አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 08/2018
በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የትምህርት ቢሮ አገልግሎት የሚውል የልብስ ስፌት ማሽን ግዥ ከዚህ በታች በቀረበው መሰረት ግዥ ለመከናወን ሕጋዊ ድርጅቶችን አወዳድሮ በግልጽ ጨረታ መግዛት ይፈልጋል።
ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
- በመስኩ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ የታክስ ክሊራንስ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥርና የታክስ ምዝገባ ምስክር ወረቀት እንዲሁም የተጫራቾች የአቅራቢነት ምዝገባ ያላቸው መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ዋጋቸውን የሚገልፀውን ሰነድ በታሸገ ፖስታ ይህ የጨረታ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 20ኛው ቀን ከቀኑ 11፡30 ድረስ ከግ/ፋ/ን/አስ/ር ዳይሬክቶሬት በአካል በመቅረብ መግዛት አለባቸው።
- የጨረታ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን በ21ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡00- 6፡00 ድረስ ብቻ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ21ኛው ቀን 9፡00 ሰዓት ይከፈታል፣ ሆኖም 16ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከላይ በተጠቀስው ጊዜና ሰዓት የሚከፈት ይሆናል፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለ90 ቀን ጸንቶ የሚቆይ ብር 50,000.00 /ሃምሳ ሺህ ብር/ በሲፒኦ ወይም አንኮንድሽናል የባንክ ዋስትና በማቅረብ መወዳደር አለባቸው።
- ተጫራቾች በሚወዳደሩበት ጊዜ በሁለት ኮፒ እና አንድ ኦርጅናል ፖስታ በማሽግ ቴክኒካል፣ ፋይናንሻል የጨረታ ዶክመንት ለየብቻ በማድረግ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በኦርጅናል ቴክኒካል ዶክመንት ውስጥ ብቻ ማቅረብ አለባቸው።
- ጨረታው ለ3 ወራት 190 ቀናት ብቻ ፀንቶ የሚቆይ ይሆናል፡፡
- የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል ከግ/ፋ/ን/አስ/ር ዳይሬከቶሬት ከግዥ ክፍል 14 ቁጥር ማግኘት ይቻላል።
- ቢሮው ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ማሳሰቢያ፡- ሽያጩ ቫትን ጨምሮ ከብር 20,000.00 /ሃያ ሺህ ብር/ በላይ ለሆነው ግዥ 50% ቫት ቀንሰን የምናስቀር መሆኑን እንገልፃለን፡፡
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡- 046-221-70-02/03 ደውለው ይጠይቁ።
የሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ትምህርት ቢሮ
