የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት በ2018 በጀት ከዚህ በታች የተዘረዘሩ የሽያጭ፤ ግዥና የአገልግሎት ግዥ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛትና ለመሸጥ ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር 004/ሽያጭና አገልግሎት/18 ዓ.ም
የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት በ2018 በጀት ከዚህ በታች የተዘረዘሩ የሽያጭ፤ ግዥና የአገልግሎት ግዥ በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛትና ለመሸጥ ይፈልጋል።
- 1ኛ የሠነድ ህትመት ግዥ ለ1ኛ ጊዜ
- 2ኛ የ2017/2018 ዓ/ም የሂሳብ ኦዲት አገልግሎት ጨረታ ለ3ተኛ ጊዜ
- 3ኛ የትራንስፖርት ማጓጓዣ አገልግሎት ጨረታ ለ3ተኛ ጊዜ
- 4ኛ ፖሊ-ባግ የዘር መቋጠሪያ ከረጢት/ ጨረታ ለ2ተኛ ጊዜ
- 5ኛ የሠራተኞች የደንብ ልብስ ግዥ ለ1ኛ ጊዜ
በዚሁ መሰረት፡-
- ተጫራቾች በሥራ ዘርፉና ሌሎች ተያያዥ ሥራዎች ህጋዊ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸውና የዘመኑን የመንግሥት ግብር አጠናቀው ስለመክፈላቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
- ተጫራቾች ለጨረታው ውድድር ከሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተመሰከረለት የክፍያ ማዘዣ (CPO) በጨረታ ሰነድ ላይ የሚገለጽ ይሆናል፡፡
- የጨረታው ሰነድ ይህ ጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 12 ኛው ቀን ድረስ የማይመለስ ብር 400.00 በመክፈል በሀዋሳ ከተማ በድርጅቱ የግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነድ ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 12 ቀናት ውስጥ በሰም በታሸገ ፖስታ /ኤንቨሎፕ/ በማድረግ ኦሪጂናልና ኮፒውን ለየብቻው ከተጓዳኝ ማስረጃዎች ጋር በማደራጀት በድርጅቱ የግዥ ፋይ/ን/አስ/ከፍል ቢሮ ቁጥር 12 ለዚሁ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ በ12ኛው ቀን እስከ 8፡00 ሰዓት ማስገባት አለባቸው፡፡
- የጨረታው ሳጥን የጨረታው ማስታወቂያ በወጣ በ12ኛው ቀን ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ታሽጐ በእለቱ በ8፡30 ሰዓት በድርጅቱ ግዥ ፋይ/ንብ/አስ/ክፍል ቢሮ ቁጥር 12 ተጫራቾች /ህጋዊ ወኪሎቻቸው/ በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ነገር ግን 12ኛው ቀን የሥራ ቀን ባይሆን በቀጣዩ የሥራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ተመሳሳይ ቦታ ሰዓትና ሁኔታ ይከፈታል፡፡
- ድርጅቱ ለዚሁ ጨረታ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎች በሚዘጋጀው የጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይቻላል፡፡
በስልክ ቁጥር 046 220 1752/2285/2117
የደቡብ ምርጥ ዘር ድርጅት
