ሞጆ በሚገኘው የድርጅቱ ዎርክ ሾፕ ውስጥ ያሉትን የተለያዩ ያገለገሉ ጎማዎችን፣ የተቃጠሉ ዘይቶችን፤ የተሸከርካሪ ባትሪዎቸ እና ሌሎች እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
የሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታው ቁጥር [Gada/NCB/06/2018]
ሞጆ በሚገኘው የድርጅቱ ዎርክ ሾፕ ውስጥ ያሉትን የተለያዩ ያገለገሉ ጎማዎችን፣ የተቃጠሉ ዘይቶችን፤ የተሸከርካሪ ባትሪዎቸ እና ሌሎች እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል። ስለሆነም በጨረታው መወዳደር የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን መስፈርቶች በሟሟላት መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን ፡፡
1. ኢትዮጵያዊ የሆነ/የሆነች እና የታደሰ የኗሪነት መታወቅያ ያለው ወይም ያላት እና በማንኛውም ንግድ ስራ ላይ የተሰማራ ወይም የተሰማራች
2. ማንኛውም ተወዳዳሪ ተጫራች የጨረታ ሰነድ ይህ ማስታወቅያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 10 ቀን አየር ላይ የሚዉል ሲሆን ሰንጋ ተራ ንግድ ስራ ኮሌጅ ፊት ለፊት ቢፍቱ አዱኛ ህንጻ 12ኛ ፎቅ ከጠዋቱ 2፡30 እሰከ 11፡00 በመምጣት የማይመለስ 100 (አንድ መቶ) ብር በመክፈል የጨረታ ሰነዱን በመግዛት መወዳደር ይችላሉ፡፡
3. ማንኛዉም ተጫራች በገዛዉ የጨረታ ሰነድ ላይ ከብ ማህተም ወይም በመፈርም በሰም በታሸገ ፓስታ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
4. ማንኛውም ተጫራች ዋጋ ሲሰጥ 15% ቫት ያካተተ መሆን አለበት:
5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ አጠቃላይ ከተወዳደሩበትን ዋጋ 2% በ ሲ.ፒ.ኦ ማቅረብ ያለባቸው ሲሆን የሞሉትን ጨረታ እንዲሁም ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በአንድ ላይ በፖስታ በማሸግ ማቅረብ አለባቸው፡፡
6. የጨረታ ሰነድ የገዙ ተወዳዳሪውች የገዙትን ሰነድ እና ደረሰኝ በመያዝ እቃዎችን ሞጆ በሚገኘው የድርጅቱ የተሽከርካሪ ማቆሚያ ግቢ ውስጥ ማየት ይቻላል፡፡
7. የጨረታ አሸናፊነቱ ከተረጋገጠ ቀን ጀምሮ ባሉት 5 ተከታታይ የስራ ቀናት አጠቃላይ ያሸነፉበትን እቃ ሙሉ በሙሉ በመከፈል እቃዉን ከጊቢ ማውጣት አለባቸው
8. ተጫራች በሚያቀርቡት ዋጋ የጨረታ መግቢያ ሰዓት ከተጠናቀቀ በኋላ ማሻሸያ ማድረግ እና እራሳቸውን ከጨረታ ማግለል አይቻልም፡፡
9. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የጨረታ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 10 ቀን አየር ላይ የሚዉል ሆኖ በıoኛዉ ቀን በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዛዉ እለት 8፡30 ላይ ተጫራቾች እና ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት የሚከፈት ይሆናል፡፡
10. ንብረቶቹ የሚገኙበት ቦታ ሞጆ ይገኛሉ፡፡
11. የጨረታ መከፈቻ ቀናት ቅዳሜ እና እሁድ እንዲሁም በበዓላት ቀን ከሆነ በሚቀጥለዉ የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት ይሆናል፡፡
12. ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። አድራሻ - ሰንጋ ተራ ንግድ ስራ ኮሌጅ ፊት ለፊት ቢፍቱ አዱኛ ህንጻ 12ኛ ፎቅ
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 011-558-25-19
ገዳ ትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ አ/ማ
