በፌዴራል ማረ/ኮሚሽን ከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማዕከል የሲቪል ሰራተኞች፣ የስፖርተኞች የሥራ ልብስና ጫማዎች እንዲሁም ለህግ ታራሚዎች አገልግሎት የሚውል ዩኒፎርም በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ከአሸናፊ ድርጅቶች መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 1) የሲቪል ሰራተኞች፤ የስፖርተኞች የሥራ ልብስና ጫማዎች እንዲሁም ለህግ ታራሚዎች አገልግሎት የሚውል ዩኒፎርም በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ከአሸናፊ ድርጅቶች መግዛት ይፈልጋል፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልግ ሁሉ፤ በሥራው መስክ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ፤ በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር በዕቃ ግዥ አገልግሎት አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ የተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) እንዲሁም ቲን ቁጥር (Tin Number) ተመዝጋቢ የሆነና ግብር ስለመክፈሉ የተሟላ ማስረጃ ሊያቀርቡ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ቁጥር-1- ለህግ ታራሚዎች አልባሳት (ዩኒፎርም) ፣ የስፖርተኞች የሥራ ልብስና ጫማዎች እንዲሁም የሲቪል ሰራተኞች የስራ ልብስን ለጨረታው ማስከበሪያ ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) በባንክ በተመሰከረለት ሲፒኦ (CPO) ከጨረታው ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች አንዱ በሌላው ተጫራች ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ ተቀባይነት የለውም፡፡
- ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያ (ፕሮፎርማቸው) በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በአራት ኮፒ አሽገው ማቅረብ አለባቸው።
- የጨረታ ቁጥር-1 ህዳር 5 ቀን 2018 ዓ/ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት የጨረታ ሰነዳቸውን በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ የግዥ ከንውን ቡድን ቢሮ ቁጥር 02 ማስገባት ይችላሉ፡፡ ጨረታው በዚሁ ዕለት ከረፋዱ 4፡15 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በማረ/ቤቱ የግዥ ክንውን ቡድን ቢሮ ቁጥር 2 ይከፈታል።
- አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉበትን ዕቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት በከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማዕከል (ገላን) በሚገኘው ግ/ቤታችን ማስረከብ አለባቸው ማረ/ቤቱ የሚገዛቸው ዕቃዎች በጨረታ ሰነዱ ተርዝረው ቀርበዋል፡፡
- ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ለእያንዳንዳቸው የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል ቃሊቲ በሚገኘው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000007971188 ቃሊቲ ማረ/ቤት እደ/ጥ/ማዕከል በሚል ገንዘቡን ገቢ ካደረጉ በኋላ የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታው ሰነድ ከተከፈተ በኋላ ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለውጥ ማድረግ እንዲሁም ከጨረታው ራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
- ተጫራቾች ፕሮፎርማቸው ላይ ዋጋ ሲፅፉ ስርዝ ድልዝ የሌለበት ጎላ ብሎ የሚነበብ ፅሑፍ መሆን ይገባዋል በአሃዝና በፈደል መፃፍ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማዕከል - ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር
011-4-39-76-61/ 011-4-39-49-16/ ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
በፌዴራል ማረ/ኮሚሽን ከፍተኛ ጥበቃ ማረሚያ ማዕከል
