Tender Detail

Tender Details

  • Company የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት (FDRE Refugees and Returnees Service)
  • Address የእንቁላል ፋብሪካ አደባባይን ሳይሻገሩ ከፌዴራል ፖሊስ ክበብ ፊት ለፊት : አዲስ አበባ ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 011 813 21 93
  • Websitehttps://rrs.et/
  • Deadline26 Nov 2025, 12:00 AM
  • magazineAddis Zemen
  • Bid Document Price200.00
  • opening date2025-11-26 00:00:00
  • Categories Vehicle , Vehicle Battery , Vehicle tire , Vehicle Spare Parts

የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ለሚገለገልባቸው ተሽከርካሪዎች የተለያየ መጠን ያላቸውን የጎማ እና ባትሪ ዓይነቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።


የጎማ ግዥ የጨረታ ማስታወቂያ

 

የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ለሚገለገልባቸው ተሽከርካሪዎች የተለያየ መጠን ያላቸውን የጎማ እና ባትሪ ዓይነቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።

ስለዚህ ተጫራቾች፦

  1. የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ፣ በጨረታ ለመወዳደር የሚያስችል ክሊራንስ ፣ህጋዊና የታደሰ ንግድ ፍቃድ፣ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ያላቸውና በጨረታው ለመሳተፍ በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያሳይ የምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው መሆን አለባቸው።
  2. የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ) በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) የስራ ቀናት ውስጥ በስራ ሰዓት ገንዘብ ያዥ ቢሮ ወይም ሂሳብ ክፍል በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ፡፡ ቅዳሜና እሁድ የመስሪያ ቤቱ የስራ ሰዓት አይደሉም።
  3. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) የስራ ቀናት ውስጥ በጨረታ ሰነዱ ላይ ለተጠቀሱት ዕቃዎች የፋይናንሺያል እና ቴክኒካል ሰነዶችን ለየብቻ በማዘጋጀት በአገልግሎቱ ዋና መስሪያ ቤት የግዥ ቡድን ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ እስከ 400 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል። የተጫራቾች ዋጋ በግልፅ የሚነበብና ስርዝ ድልዝ የሌለው መሆን ይኖርበታል፡፡ ስርዝ ድልዝ ያለበት የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት አይኖረውም።
  4. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10ኛው ስራ ቀን ከጠዋቱ 400 ተዘግቶ በዚያው ዕለት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከጠዋቱ 430 ይከፈታል።
  5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ተጨማሪ እሴት ታከስን ጨምሮ የሚቀርቡትን አጠቃላይ ዋጋ 2% (ሁለት በመቶ) ለስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት (Refugees and Returnees Service) በሚል የተዘጋጀ የባንክ ማዘዣ (CPO) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ጋራንቲ (unconditional Bank Guarantee) ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
  6. የጨረታው አሸናፊ ውል በሚፈርምበት ወቅት የመልካም ስራ አፈፃጸም ማስከበሪያ /Performance Bond/ እቃዎቹን ለማቅረብ ያሸነፈበትን አጠቃላይ ዋጋ 10% (አስር በመቶ) ለስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት (Refugees and Returnees Service) በሚል በተረጋገጠ የባንከ ማዘዣ (CPO) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንከ ጋራንቲ (unconditional Bank Guarantee) ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
  7. የጨረታው አሸናፊ ጥሪው በደረሰው 10 ቀናት ውስጥ በአገልግሎቱ ዋና መስሪያ ቤት ቀርቦ የስራ ውል መፈረም አለበት።
  8. አሸናፊው ጥሪ በደረሰው በአስር ቀናት ውስጥ በአገልግሎቱ ዋና መስሪያ ቤት ቀርቦ ውል ካልፈረመ አሸናፊነቱ ተሰርዞ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ለመስሪያ ቤቱ ገቢ ይሆናል።
  9. አገልግሎት መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

አድራሻ - የእንቁላል ፋብሪካ አደባባይን ሳይሻገሩ ከፌዴራል ፖሊስ ክበብ ፊት ለፊት

ስልክ ቁጥር 09-97-23-66-31

የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት

Save Tender