የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የወንድ ቦት ጫማ ከነዚፑ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት አስፈልጓል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የወንድ ቦት ጫማ ከነዚፑ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት አስፈልጓል፡፡
|
ተ/ቁ |
የዕቃው ዓይነት |
|
1 |
የወንድ ቦት ጫማ ከነዚፑ |
በመሆኑም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት አለባችሁ።
- በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው መሆን በዘርፉ የተሰማሩ ለመሆናቸው በጀርባው የተገለጸ መሆን አለበት፡፡
- የዘመኑን የመንግስት ግብር የከፈሉ፡፡
- ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆነ፣ የታደሰ የዘመኑ ንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉና የታደሰ የንግድ ምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ አለባቸው።
- የመንግስት መ/ቤቶች ለሚያመጡት ጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል የአቅራቢዎች የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ አለባቸው እንዲሁም በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል ከገቢዎች ጉምርክ ባለስልጣን የዘመኑ ግብር ከፍለው ስለማጠናቀቃቸው ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- አማራጭ ዋጋ በዚህ ጨረታ ማቅረብ አይቻልም።
- በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ሁሉ የጨረታ ውጤቱ እንደታወቀ ተመላሽ የሚሆን የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለፌዴራል ማረ/ቤት ኮሚሽን ተብሎ በተዘጋጀው ከባንክ በተመሰከረበት ሲ.ፒ.ኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ እንዲሁም የባንክ ዋስትና የሚያስይዙ ተጫራቾች የቆይታ ጊዜው ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ የሚቆጠር 150 ቀንና ከዚያ በላይ መሆን ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች ቴክኒካል ሰነዶችና የዋጋ ማቅረቢያዎችን /ፋይናንሻል/ ሰነዶችን በተለያዩ ፖስታ ታሽጎ ለየብቻ መቅረብ አለበት ቴክኒካልና ፋይናንሻል ሰነድ በአንድ ላይ አሽጎ ያቀረበ ተወዳዳሪ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከጨረታው ውጭ ይደረጋል፡፡
- ማንኛውም ተጫራቾች የሚያስገባው ሰነድ ፋይናንሻል የጨረታ ሰነድ አንድ ኦርጅናልና አንድ ኮፒ በተለያዩ ፖስታ በሰም በማሸግ በፖስታው ላይ የጨረታ ሰነዱን ቁጥር የሚጫረትበትን በትክክል መጻፍ እንዲሁም በፖስታው ላይ እና በሁሉም የመጫረቻ ሰነድ ላይ የድርጅቱን ማህተም በመምታት ማስገባት ያለበት ሲሆን ስርዝ ድልዝ በፍሉድ የጠፋ ሰነድ ዋጋ ያልተሞላበት ዝርዝር ተቀባይነት የለውም።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚያሲዙት ሲ.ፒ.ኦ ከቴክኒከ ሰነዶች ጋር በአንድ ላይ ታሽገው መቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች አ/አበባ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ከፍ ብሎ በሚገኘው ፌዴራል ማረ/ቤት ኮሚሽን ዋናው መ/ቤት 1ኛ ፎቅ የፋይናንስ አስ/ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቀርበው በእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመሰስ ብር .... /ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው በ 29/3/2018 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ታሽጎ ከቀኑ 4፡30 ሰዓት ሲሆነ በመ/ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
- ዘግይተው የሚመጡ የጨረታ ሰነዶች ተቀባይነት የላቸውም፤
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ በከፊልም ሆነ በሙሉ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን ዕቃዎች እስፔስፊኬሽን ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይችላሉ፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 01-11-26-56-65 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
በፍትህ ሚኒስቴር የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን
