Tender Detail

Tender Details


በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን በ2018 በጀት ዓመት የሚሆኑ የዕቃ እና የአገልግሎት ግዥዎች ከዚህ በታች በተዘረዘረው መሠረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።


 

የጨረታ ማስታወቂያ

ብሔራዊ ግልፅ ጨረታ //////.002/2018

 

የግልፅ ጨረታ ግዢ ማስታወቂያ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን 2018 በጀት ዓመት የሚሆኑ የዕቃ እና የአገልግሎት ግዥዎች ከዚህ በታች በተዘረዘረው መሠረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

 

.

ሎት

የግዥው ዝርዝር

ጨረታው የወጣበት ጊዜ

የግዥው ዓይነት

የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና መጠን

1

1

የጽህፈት መሳሪያዎች

ለመጀመሪያ ጊዜ

ዕቃ

20,000

2

2

የፓራሚሊተሪ ሰራተኞች እና የአስተዳደር ሰራተኞች ደንብ ልብስ

ለሁለተኛ ጊዜ

ዕቃ

50,000

3

3

የአደጋ ጠላቂ ዋናተኞች እቃዎች እና ብሪዚንግ አፓራተስ፤

ለሁለተኛ ጊዜ

ዕቃ

100,000

4

4

ልዩ ልዩ የእጅ መሳሪያዎች፤

ለሁለተኛ ጊዜ

ዕቃ

20,000

5

5

ኤሌክትሮኒክስ እቃዎችጀነሬተር እና የአዳራሽ ሳውንድ ሲስተም ከነሙሉ እቃው ተገጥሞ

ለሁለተኛ ጊዜ

ዕቃ

60,000

6

6

የህጻናት ማቆያ እቃዎችየተለያዩ መጋረጃዎች እና የፕላስቲክ ወንበሮች

ለመጀመሪያ ጊዜ

ዕቃ

20,000

7

7

የተሸከርካሪ መለዋወጫ እና ጎማዎች

ለሁለተኛ ጊዜ

ዕቃ

50,000

8

8

የህክምና እቃዎች ግዥ

ለሁለተኛ ጊዜ

ዕቃ

40,000

9

9

የህትመት ውጤቶች

ለሁለተኛ ጊዜ

አገልግሎት

30,000

10

10

ምግብ ነክ የሆኑና ምግብ ነክ ያልሆኑ

ለሁለተኛ ጊዜ

ዕቃ

40,000

11

11

የጽዳት እቃዎች /የዱቄት ሳሙና/

ለሁለተኛ ጊዜ

ዕቃ

20,000

 

ተወዳዳሪዎች ማሟላት ያለባቸው መስፈርቶች

  • ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፤ ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ማንኛውም ህጋዊ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርት አሟልተው በጨረታው መወዳደር ይችላል።
  1. አግባብነት ያለው ህጋዊ በዘርፉ የተሰጠ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያለቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ
  2. የቫት ተመዝጋቢ መሆኑን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
  3. ዋና ንግድ ምዝገባ ፍቃድ እና ያቅራቢዎች ምዝገባ በዌብ ሳይት መመዝገቡን የሚያሳይ ምስክር ወረቀት ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ።
  4. በጨረታው ለመሳተፍ የሚያስችል ከገቢዎችና ጉምሩክ ኮሚሽኑ ክሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ
  5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በሁሉም ሎት በተቀመጠው ሲፒዮ (CPO) ገንዘብ መጠን መሰረት ኦርጅናል ቴክኒካል ፕሮፖ ውስጥ ወይም ለብቻው ፖስታ በማድረግ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እሳትና ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን /ADDIS ABABA CITY ADMINISTRATION FIRE & DISASTER RISK MANAGEMENT COMMISSION በሚል ስም በማሰራት በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም የባንክ ጋራንቲ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
  6. ተጫራቾች የሚያቀርቡትን የዋጋ መግለጫ ዋናና ኮፒ እንዲሁም የቴክኒክ መግለጫ ዋናና ኮፒ በማድረግ በአጠቃላይ 2 /ሁለት/ ኦርጅናል እና 2/ሁለት/ ኮፒዎች፤ ቴክኒካል ፕሮፖዛልና ፋይናሻሉን ለየብቻ ኤንቨሎፕ በማድረግ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በኮሚሸኑ መንግስት ግዥ ዳይሬቶሬት ሥራ ክፍል ማስገባት አለባቸው።
  7. 100,000.00 /መቶ ሺህ ብር/ በላይ ከተጫረቱ የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን ማስረጃ ፎቶ ኮፒ ማያያዝ ይኖርባቸዋል።
  8. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 የሥራ ቀናት ውስጥ በእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በመፈል የጨረታውን ሠነድ በሥራ ሰዓት የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ፋይናንስ ዳይሬክቶሬት 1 ፎቅ ቢሮ ቁጥር 59 መውሰድ ይችላሉ።
  9. ተጫራቾች በገዙት ሰነድ መሠረት የሚወዳደሩበትን ቴክኒካልና ፋይናሻሉን ሰነድ ብቻ ለየብቻ በሰም በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት አሥር ተከታታይ የሥራ ቀናት በተሰጠው ቢሮ ለጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት የሥራ ቀን 11ኛው ቀን ከቀኑ 400 ሰዓት ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸውን በተገኙበት 11ኛው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 430 ሰዓት ይከፈታል ሆኖም።
  • ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በዓል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ ወደ ሚቀጥለው የሥራ ቀን ይዘዋወራል

 

ለተጨማሪ መረጃ - 011 878 76 86 በመደወል መረጃ ማግኘት ይቻላል።

አድራሻ - አዲስ አበባ /ጊዮርጊስ ፊት በሚገኝ እሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን 1 ፎቅ ህንፃ ቢሮ ቁጥር 59 ማግኘት ይቻላል።

 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን

 

Save Tender