የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በ2018 ዓ.ም ለቢሮ አገልግሎት የሚውል ዕቃዎችና አገልግሎቶች፣ ውሃ፣ የአየር ሰዓት እና የጥናትና ምርምር አገልግሎት ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ 001/2018
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በ2018 ዓ.ም ለቢሮ አገልግሎት የሚውል ዕቃዎችና አገልግሎቶች፣ ውሃ፣ የአየር ሰዓት እና የጥናትና ምርምር አገልግሎት ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚሁ መሰረት መጫረት የምትፈልጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባችኋል፡፡
- ተጫራቾች በዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ የቫት ሰርተፍኬት፣ ቲን ሰርተፍኬት እና በዘርፉ የተሰማሩ መሆናቸውን ማስረጃ እና ተያያዥ ሰነዶችን ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ለጥናትና ምርምር ቴክኒካል ኦርጅናልና ኮፒ፤ ፋይናንሽያል ኦርጅናልና ኮፒ እንዲሁም CPO በአንድ ፖስታ ለብቻው በማሸግ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ለዕቃና ሌሎች አገልግሎቶች በየሎቱ ኦርጅናልና ኮፒ ብቻ በማድረግ አሽገው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን አንዱን ሎት ከሌላ ሎት ቀላቅለው ካቀረቡ ከጨረታው ውጪ ይሆናል፡፡
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን አንስቶ ለተከታታይ አስር /10/ የስራ ቀናት አየር ላይ የሚውል ሆኖ በአስራ አንደኛው ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 4፡00 /አራት ሰዓት/ ታሽጎ 4፡30 /አራት ተኩል/ ይከፈታል፡፡ በ11ኛው ቀን በዓል ከሆነ በቀጣይ የስራ ቀን በተጠቀሰው ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተመሰከረለት CPO በባለስልጣኑ ስም ከታች በሰንጠረዥ የተገለፀውን የገንዘብ መጠን ማስያዝ አለባቸው።
- ባለስልጣኑ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። አማራጭ ጨረታ ተቀባይነት የለውም፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስታወቂያው ላይ በተገለፁት የጨረታ ዓይነቶች በሙሉ ወይም በከፊል መጫረት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ከፋይናንስ ዳይሬክቶሬት ቀርበው ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 /አስር/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ዘወትር በሥራ ሰዓት ቢሮ ቁጥር 403 መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ናሙና ማቅረብ የማይቻልባቸው ለትልልቅ ዕቃዎች ከለር ፎቶ ተያይዞ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች የዕቃው /የአገልግሎት/ ግዥ ዝርዝር በክፍል 6 ላይ የተቀመጠውን ሰነድ ላይ ዋጋው ተሞልቶና የድርጅቱ ማህተም እና ፊርማ ተደርጎ መቅረብ አለበት፡፡
- ናሙና ለሚያስፈልጋቸው ሎቶች ጨረታ ከመከፈቱ በፊት በካርቶን/በማዳበሪያ አድርጎ መቅረብ አለበት።
- ተጫራቹ አሸናፊ በሚሆንበት ወቅት ለናሙና ያቀረበው ዕቃና የሚያስገባው ዕቃ 100% መመሳሰል አለበት፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳችሁን አሽጋችሁ በጨረታ ሳጥን ውስጥ ከአስገባችሁ በኋላ የዋጋ ማስተካከያ ወይም ከጨረታው ለመውጣት ከፈለጋችሁ ጨረታው ከመከፈቱ በፊት በደብዳቤ ማሳወቅ አለባችሁ።
- ተጫራቾች ከባለስልጣኑ በገዙት ሰንድ ላይ ብቻ የአንዱን ዋጋ ከነቫቱ እንዲሁም ጠቅላላ ዋጋ ከነቫቱ እንዲሁም ጠቅላላ ዋጋ ከነቫቱ ተሞልቶ መቅረብ አለበት፡፡
የጨረታ ማስከበሪያ ዝርዝር ሰንጠረዥ
|
ተ.ቁ |
የሎቶች ዝርዝር |
ሎት |
ብር |
ሣ |
|
1 |
የጥናትና ምርምር |
ሎት-01 |
10,000 |
00 |
|
|
ዕቃና ሌሎች አገልግሎቶች ዝርዝር |
ሎት |
|
|
|
1 |
የደንብ ልብስ |
ሎት-1 |
2,000 |
00 |
|
2 |
የፅዳት ዕቃዎች |
ሎት-2 |
2,000 |
00 |
|
3 |
አላቂ የጽህፈት መሳሪያዎችና ቶነር ዕቃዎች |
ሎት-3 |
5,000 |
00 |
|
4 |
ITና ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች |
ሎት-4 |
5,000 |
00 |
|
5 |
የቤት/ኪችን/ ዕቃዎች |
ሎት-5 |
3,000 |
00 |
|
6 |
የቢሮ ምንጣፍ መጋረጃ |
ሎት-6 |
2,000 |
00 |
|
7 |
የህንፃ መሳሪያዎች |
ሎት-7 |
2,000 |
00 |
|
8 |
ህትመት |
ሎት-8 |
5,000 |
00 |
|
9 |
የአየር ሰዓት አገልግሎት ግዥ |
ሎት-9 |
5,000 |
00 |
|
10 |
የመኪና ዕቃዎች |
ሎት-10 |
2,000 |
00 |
|
11 |
ግማሽ ሊትር ውሃ |
ሎት-11 |
1,000 |
00 |
|
12 |
የልብስ ስፌት |
ሎት-12 |
1,000 |
00 |
- መስሪያ ቤቱ ጨረታውን 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን ዕቃዎች እና አገልግሎቶች ለባለስልጣኑ በራሳቸው ትራንስፖርት ግዥ ፈፃሚው መስሪያ ቤት ንብረት ክፍል ድረስ ማቅረብ ሲኖርባቸው ቅርንጫፍ /ጽ/ቤቶችን በተመለከተ ራሳቸው ሔደው ከአሸናፊው ድርጅት የሚረከቡ ይሆናል፡፡
- የመንግስት ተቋማት ለጥናትና ምርምርና ለአየር ሰዓት ግዥ (ንግድ ፈቃድ፣ ቲን ሰርተፊኬት፣ CPO) ማቅረብ አስገዳጅ ላይሆን ይችላል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 011-126-53-66 ደውሎ መጠየቅ ወይም የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አራት ኪሎ አራዳ ክፍለ ከተማ ጎን ቢማሂ ሪል እስቴት ህንፃ 4ኛ ፎቅ የመንግስት ግዥ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 403 በአካል ቀርበው ማነጋገር ይችላሉ፡፡
የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን
