ሳሪስ ጤና ጣቢያ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት እቃዎችን በግልጽ ጨረታ መለያ ቁጥር 02/2018 አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ሳሪስ ጤና ጣቢያ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት እቃዎችን በግልጽ ጨረታ መለያ ቁጥር 02/2018 አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
- ሎት 1 የሰራተኛ ደንብ ልብስ
- ሎት 2 የተለያዩ ህትመት ሥራዎች
- ሎት 3 የተለያዩ የፅዳት እቃዎች
- ሎት 4 የኤሌክትሮኒክስ ጥገና እና ሰርቪስ ሥራዎች
- ሎት 5 የጥገና እቃዎች ግዥ
- ሎት 6 መድሃኒት ግዥ
- ሎት 8 የሕክምና መሳሪያ ግዥ
- ሎት 9 ቋሚ እቃዎች ግዥ
- ሎት 10 የጄኔሬተር ዘይት ግዥ
- ሎት 11 የጄኔሬተር እቃ ግዥ እና ጥገና
- ሎት 12 የተለያዩ ክፍሎች ጥገና እና እድሳት ሥራ
- ሎት 13 የህፃናት መጫዎቻ እቃዎች ግዥ
- ሎት 14 የአይቲ እቃዎች ግዥ
- ሎት 15 የመኪና እቃዎች ግዥ
ከላይ የተዘረዘሩትን እቃዎች ላይ መጫረት የምትፈልጉ ተጫራቾች
- በዘርፉ ህጋዊ ፍቃድ ያላቸው የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆናቸውን የሚገልፅ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣ የንግድ ምዝገባና ምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይነት የምስክር ወረቀት ያላቸው፣ ጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ የምስክር ወረቀት ያላቸው እና ቫት ተመዝጋቢ (VAT) መሆናቸውን የሚገልፅ የምስክር ወረቀት እነዚህን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 10 የሥራ ቀናት የጨረታ ሰነዱን ከሳሪስ ጤና ጣቢያ ከፋ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 35 የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋጋ ማለትም ሎት 1 (ደንብ ልብስ) 41,968.24 (አርባ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ስልሳ ስምንት ብር ከ24/100) ፤ ሎት2 (የተለያዩ ህትመት ስራዎች) 396.00 (ሶስት መቶ ዘጠና ስድስት ብር ብቻ) ፣ ሎት 3 (የተለያዩ የዕዳት እቃዎች) 4,111.13 (አራት ሺህ አንድ መቶ አስራ አንድ ብር ከ13/100)፣ ሎት 4 (የኤልክትሮኒክስ ጥገና እና ሰርቪስ)፣ 1,553.34 (አንድ ሺህ አምስት መቶ ሃምሳ ሶስት ብር ከ34/100)፣ ሎት 5 (የጥገና እቃዎች ግዥ) 669,33 (ስድስት መቶ ስልሳ ዘጠኝ ብር ከ33/100)፤ ሎት 6 (የመድሃኒት ግዥ) 36,000.00 (ሰላሳ ስድስት ሺህ ብር ብቻ)፣ ሎት 7 (ሪኤጀንት ግዥ) 40,000.00 (አርባ ሺህ ብር ብቻ)፣ ሎት 8 (የህክምና መሳሪያ ግዥ) 76,000.00 (ሰባ ስድስት ሺህ ብር)፣ ሎት 9 (ቋሚ የቢሮ እቃዎች) 4,473.90 (አራት ሺህ አራት መቶ ሰባ ሶስት ብር ከ90/100)፣ ሎት 10 (የጄኔሬተር ዘይት ግዥ) 1246.00 (አንድ ሺህ ሁለት መቶ አርባ ስድስት ብር ብቻ) ፣ሎት 11 (የጀኔሬተር እቃ ግዥ እና ጥገና) 3,468.67 (ሦስት ሺህ አራት መቶ ስልሳ ስምንት ብር ከ67/100)፤ ሎት 13 የህፃናት መጫወቻ እቃዎች ግዥ 1418.00 (አንድ ሺህ አራት መቶ አስራ ስምንት)፤ ሎት 14 (የአይቲ እቃዎች ግዥ) 6,049.00 (ስድስት ሺህ አርባ ዘጠኝ ብር ብቻ) እና ሎት 15 (የመኪና እቃዎች ግዥ) 11,576.94 (አስራ አንድ ሺህ አምስት መቶ ሰባ ስድስት ብር ከ94/100 በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም ሲፒኦ (CPO) በአድራሻችን ከጨረታ ሰነድ ጋር በፖስታ በማሸግ ማቅረብ አለባቸው::
- ተጫራቾች በዚህ ጨረታ ተወዳድረው አሽናፊ ከሆኑ የአሸነፈው ድርጅት የውል ማስከበሪያ ጠቅላላ 10% ለሥራ አፈፃጸም ዋስትና በቅድሚያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 10ኛው የስራ ቀን አየር ላይ ውሎ በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ታሽጎ በዛኑ ቀን ከጥዋቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸቸው ባሉበት ሳሪስ ጤና ጣቢያ ቢሮ ቁጥር 31 ይከፈታል። ነገር ግን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ባይገኙም የጨረታ ሂደት በተቀመጠው መሰረት ይካሄዳል። የጨረታ መዝጊያ እና መክፈቻ ቀን ዝግ ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይሆናል።
- ተጫራቾች ከመስሪያ ቤቱ በገዙት የጨረታ ሰነድ ላይ ብቻ የዋጋ ዝርዝር ሞልተው ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ለሚወዳደሩት እቃዎች ሣምፕል ሙሉ በሙሉ ጨረታ ከመከፈቱ በፊት ማቅረብ ይጠበቅበታል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሙሉ ሰነድ ዋናውንና ፎቶ ኮፒውን በመለየት የመስሪያ ቤታችሁን ማህተም በማድረግ እና በእያንዳንዱ ሰነድ ላይ ፊርማቸውን በመፈረም በታሸገ ፖስታ ማቅረብ ይኖርባችዋል።
- ጥቃቅን እና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች በሀገር ውስጥ ምርት ላይ ሲወዳደሩ አምራች መሆናቸውን የሚገልፅ መረጃ ወይም ከሀገር ውስጥ አምራች ጋር የተፈፀመ ትስስር ደብዳቤ ማቅረብ ይኖርባቸዋል እንዲሁም ካደራጃቸው አካል የድጋፍ ደብዳቤ ሲኖራቸው የጨረታ ማስከበሪያ ፤ የውል ማስከበሪያ እና የቅድመ ክፍያ ዋስትና ማስያዝ አይጠበቅባቸውም። ሰነድ በነፃ የሚወስዱ ከሀገር ውስጥ አቅራቢዎች ጋር በሚያደርጉት ውድድር 3% ልዩ አስተያየት ይደረግላቸዋል።
- ተጫራቾች ዋጋ ሲሞሉ ስርዝ ድልዝ ካለው የተሠረዘው እቃ ከጨረታ ውጪ ይሆናሉ።
- ተጫራቾች ዋጋ ሲሞሉ መስሪያ ቤቱ ባወጣው እስፔከ መሠረት ብቻ ነው፣ እስፔኩን በራሳቸው የቀየሩት እቃ ከጨረታ ውጭ ይሆናል።
- ተጫራቾ ዋጋ ሲሞሉ ቫትን አካቶ መሆን አለበት።
- በመድሃኒት፣ በሪኤጀንትና የህክምና መሣሪያዎች የሚያቀርቡ ድርጅቶች የቫት ሰርተፊኬት ማቅረብ ግዴታ አይሆንም፤
- የህክምና መሣሪያዎች የሚወዳደሩ ድርጅቶች ለሚወዳደሩበት ለእያንዳንዱ የህክምና መሳሪያ EFDA PRODUCT ሰርተፊኬት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፤
- ለመድሃኒት ሪኤጀንት አቅራቢዎች የታደሰ EFDA ሰርተፊኬት ማቅረብ አለባቸው።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፈል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ሳሪስ 3F ፊት ለፊት ከሙኒክ ሆቴል አጠገብ ስልክ፡- 0114-70-98-59/0114-70-79-77
- ሎት 12 የክፍሎች ጥገናና እድሳት ሥራ
በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ የጤና ጽ/ቤት ወረዳ 6 ሳሪስ ጤና ጣቢያ ከዚህ በታች የተጠቀሰውን ሥራ ለስራው አስፈላጊ የሆኑ ግብዓቶችን በማሟላት የሚሰሩ ሥራ ተቋራጮች ማህበራት በጨረታ አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል።
|
ሎት |
የሥራው መጠርያ |
ወረዳ |
የሚጋብዘው የሥራ ተቋራጭ ደረጃ |
የፕሮጀክቱ መጠናቀቅያ ጊዜ |
የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና |
|
12 |
የተመላላሽ ህክምና ክፍል እድሳት ሥራ |
6 |
የእድሳት ደረጃቸው አነስተኛ መብቃት የሆኑ ብቻ |
45 ቀን |
ከተደራጁበት ወረዳ ዋስትና ደብዳቤ |
- በ2018 በጀት ዓመት የሚያገለግል የእድገት ደረጃ፣ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ ዓመታዊ አዲት ያስደረገ እና የገቢዎች ክሊራንስ ማቅረብ የሚችል እንዲሁም ከተደራጁበት ወረዳ መደራጀታቸውን እና የተጠቀሱት መረጃው ትክክል መሆኑን የሚገልጽ ከወረዳው ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል ኢንተርፕራይዝ
- የዘመኑ የታደሰ ስራ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ
- የግብር መለያ ቁጥር (TIN NO) ያላቸው መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ
- የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል
- የሲኦሲ (COC) ምዘና ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርባቸዋል
- በዲግሪ ተመርቀው በትምህርት ማስረጃቸው የተደራጁ ማህበራት የሲኦሲ (COC) የሙያ ብቃት ማረጋገጫ አይጠየቁም
- የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል
- መስሪያ ቤቱ ወቅታዊ ዋጋን አላገናዘቡም ብሎ ላመነባቸው የነጠላ ስራ ዋጋዎች ወቅታዊ የዋጋ ስሌት (Cost Break Down) ማቅረብ የሚችሉ (የተጠየቀውን ወቅታዊ ዋጋ ስሌት (Cost Break Down) ማቅረብ የማይችሉ ተሳታፊዎች የጨረታ ሰነዳቸው ውድቅ ይደረጋል።
- ተጫራቾች ለስራ ዝርዝሮቹ ያቀረቡት ዋጋ ወቅታዊ ዋጋን ያላገናዘበ ከሆነ ተጫራቹን ከጨረታው ያሰርዛል።
- ተጫራቾች ከተደራጁበት ክ/ከተማ የጥ/አ/ኢ/ል/ጽ/ቤት የተሰጣቸውን የደረጃ እድገት ኮፒና ኦርጂናል ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች በጨረታው ላይ ለመሳተፍ በአቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማም ሆነ በተደራጁበት ክ/ከተማ ውስጥ በእጃቸው ላይ ስራ አለመኖሩን እና ስራም ካላቸው ከ70% በላይ ማጠናቀቃቸውን የሚገልጽ ደብዳቤ ከክ/ከተማው ዲዛይን እና ግንባታ ስራዎች ጽ/ቤት ማቅረብ ይኖርባቸዋል
- አሸናፊ ማህበራት ከተደራጁበት የጥ/አ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ለቅድመ ክፍያ ዋስትና ማቅረብ አለባቸው
- ተጫራቾች በአንድ ቀን የጋዜጣ ማስታወቂያ ላይ ለወጡ የተለያዩ የክ/ከተማው ስራዎች አንድ ማህበር መሳተፍ የሚችለው በአንድ ጨረታ ላይ ብቻ መሆኑን አውቀው የሚወዳደሩበትን ጨረታ መምረጥ ይኖርባቸዋል። ከአንድ ጨረታ በላይ ወስደው የተገኙ ተጫራቾች ከውድድር ውጪ ይደረጋሉ።
- የጨረታ ሰነዱን ከሳሪስ ጤና ጣቢያ ቢሮ ቁጥር 35 ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት አለት አንስቶ እስከ 10ኛው ቀን ከላይ የተዘረዘሩትን ዋና እና ኮፒ በመያዝ ዘወትር በስራ ቀንና ሰዓት ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የወሰዱትን የጨረታ ሰነድ ሙሉ በሙሉ ሳይገነጣጠል ተመላሽ ማድረግ ይጠበቅባቸዋል:: ምንም አይነት ስርዝ ድልዝ ሰነድ ተቀባይነት የለውም:: የተሞላው የጨረታ ሰነድ አንድ ዋና እና ሁለት ኮፒ (እያንዳንዳቸው የታሸጉ እና በእያንዳንዳቸው ውስጥ የንግድ ፈቃድና የቫት ሰርተፊኬት ኮፒ የተካተተባቸው እና በእያንዳንዱ ገፅ ማህተም የተመታበት) በማድረግ ሁሉንም ሰነዶች በአንድ እናት ፖስታ በማሸግ ሳሪስ ጤና ጣቢያ ቢሮ ቁጥር 35 ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ዕለት አንስቶ እስከ 11 (አስራ አንደኛው) ቀን የጨረታ መመሪያው በሚያዘው መሰረት የጨረታ ሰነዱን ሁሉንም ሰነዶች በአንድ እናት ፖስታ በማሸግ እስከ ጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ባለው ጊዜ ማስገባት ይኖርባቸዋል:: ኦርጅናሉ ላይ ኦርጅናል፣ ኮፒዎቹ ላይ ኮፒ በማለት መጻፍ ያለባቸው ሲሆን፣ ይህን አለማድረግ ከውድድር ያሰርዛል።
- ጨረታው በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ላይ ቢሮ ቁጥር 31 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የፋይናንሻል ጨረታ ሰነድ ይከፈታል።
- ተጫራቾች የሚቀጥሯቸው ሰራተኞች በCOC ተመዝነው ሰርተፊኬት ያላቸው መሆን እና ያልተመዘኑም ከሆነ በCOC ለማስመዘን ዝግጁ እና ትብብር የሚያደርግ መሆን ይጠበቅበታል
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- መስሪያ ቤቱ ምንም አይነት ስርዝ ድልዝ ሰነድ የማይቀበል መሆኑን እየገለጽን ስርዝ ድልዝ የተገኘበት ሰነድ ከጨረታው ውጪ የሚሆን መሆኑን እንገልጻለን።
- የጨረታውን መመሪያ አለማከበር እና ከላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች አለማሟላት ከተወዳዳሪነት ያሰርዛል።
አድራሻ፡- ሳሪስ 3F ፊት ለፊት ከሙኒክ ሆቴል አጠገብ ስልክ፡- 0114-70-98-59 / 0114-70-79-77
በአቃቂ ቃሊት ክ/ከተማ የሳሪስ ጤና ጣቢያ
