የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አስተዳዳር የፋይናንስ ጽ/ቤት የግዥ የስራ ሂደት በ 2018 በጀት ዓመት በወረዳ ውስጥ ለሚገኝ ባለ በጀት መ/ቤቶች በበጀት ዓመቱ ለሚያከናውነው የእቃና አገልግሎት ግዥ ለመፈፀም በሎት /ምድብ/ የግዥ አይነቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር ኮ/ቀ/ክ/ከ/ወ/4/ፋ/የጨ/ቁ 002/18
የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አስተዳዳር የፋይናንስ ጽ/ቤት የግዥ የስራ ሂደት በ 2018 በጀት ዓመት በወረዳ ውስጥ ለሚገኝ ባለ በጀት መ/ቤቶች በበጀት ዓመቱ ለሚያከናውነው የእቃና አገልግሎት ግዥ ለመፈፀም በሎት /ምድብ/ የግዥ አይነቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
- ሎት 1. አላቂ የቢሮ እቃዎች (ስቴሽነሪ) ግዥ
- ሎት 2. የጽዳት እቃዎች ግዥ
- ሎት 3. የደንብ ልብስ ግዥ
- ሎት 4. የመድረክ ዲኮር
- ሎት 5. ቋሚ ዕቃ
በመሆኑም መ/ቤታችን ከላይ ከተራ ቁጥር 1-5 በተዘረዘሩት የግዥ ምድቦች መወዳደርና መጫረት የሚፈልግ ማንኛውም ህጋዊ ተጫራች /አቅራቢ/ አወዳድሮ ግዥውን ለመፈፀም ይፈልጋል፡፡
- የዘመኑ ህጋዊ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ ያለው እና የንግድ ምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የግብር ከፋይነት ማረጋገጫ ሰርተፍኬት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገበ እና ተጫራቾች የተመዘገቡበትን ኮፒ ማቅረብ የሚችል፡፡
- ተጫራቾች ተጨማሪ እሴት ታክስ /ቫት/ ተመዝጋቢዎች መሆን አለባቸው::
- የሚቀርበው የዋጋ ሰነድ ቫትን ያካተተ መሆን አለበት፡፡
- ጨረታው ሲከፈት የጨረታ ማስከበሪያ ሎት1:- 9,505፣ ሎት2:- 7,703.14፣ ሎት3:- 3,413፣ ሎት4- 2,000 ሎት5፡- 9,777 ለእያንዳንዱ ሎት በአድራሻችን በCPO መቅረብ አለበት፡፡
- በስራ ክህሎት የተደራጁ ኢንተርፕራይዝ ከሆነ በተደራጁበት ዘርፍ ላይ ብቻ ልዩ ድጋፍ የሚደረግላቸው ሲሆን ካደራጃቸው ጽ/ቤት ኃላፊ በተፈረመ የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ አለባቸው። ከስራ ዘርፍ ውጭ ለሆኑት እንደማንኛውም ነጋዴ የሚስተናገዱ ይሆናል፡፡
- አሸናፊው ተጫራች በሰነዱ ውስጥ በተመለከተው የጊዜ ገደብ ውስጥ ቀርቦ ውል መዋዋል አለባቸው፡፡:
- ማንኛውም ተጫራች የሚያቀርበውን ሰነድ ዋናውን እና ፎቶ ኮፒውን በየሎቱ በታሸገ ፖስታ በማድረግ ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ማስገባት ይችላሉ፡፡
- ከሎት 1-5 ለተገለጹት ዕቃዎች ሰነዱን በሚያስገቡበት ቀን ናሙና ማቅረብ አለባቸው፡፡ ናሙና ያላቀረበ ድርጅት ከውድድር ውጪ ይሆናል፡፡እቃው በናሙናው ላይ ያለውን የጥራት ደረጃ ይዞ ካልተገኘ ተመላሽ ይደረጋል፡፡
- ገዢው አካል የሚገዛውን እቃ እስከ 20% ሊጨምር ወይም ሊቀንስ ይችላል፡፡
- ለአሸናፊ ተጫራቾች በሰነድ ውስጥ የተካተተውን ጊዜ ገደብ ውስጥ ማለትም እስከ 10 ቀን ድረስ ቀርበው የውል ማስከበሪያ አሸናፊ ድርጅት ያሸነፉበትን እቃ 10% ሲፒዮ አሰርተው ውል መዋዋል አለባቸው::
- ተጫራቾች ተወዳድረው ያሸነፉባቸውን እቃዎች በወቅቱ ማቅረብ ካልቻሉ ያስያዙት ሲፒኦ ይወረሳል /ተመላሽ አይደረግም/፡፡
- የእቃ ማስረከቢ በኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 04 የፋይናንስ ጽ/ቤት የግዥ/ንብረት/ አስተዳደር ይሆናል፡፡
- በሚቀርበው የመወዳደሪያ ሀሳብ ላይ የድርጅቱ ሀላፊ ወይም ህጋዊ ውክልና ያለው ከውክልናው ደብዳቤ አያይዞ ስምና ፊርማ የድርጅቱ አድራሻ እና ስልክ ቁጥር መኖር አለበት፡፡
- መ/ቤቱ ተገቢ ነው ብሎ ካመነበት ከጨረታው አሸናፊ ድርጅት ጋር እስከ 6ወር ድረስ ውሉን ባያድስም የመግዛት መብቱ የተጠበቀ ነው::
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ከወጣበት የመጀመሪያው ቀን አንስቶ ለሚቆጠር 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ድረስ ክፍት ሆኖ ይቆይና በ11ኛው ቀን ጠዋት 4፡00 ሰዓት ታሽጎ 4:30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኮ/ቀ/ክ/ከተማ ወረዳ 04 የፋይናንስ ጽ/ቤት የግዥ ስራ ሂደት ቢሮ ውስጥ ይከፈታል፡፡
- የዕቃ ማጓጓዣ ብር አሸናፊው ተጫራች ይሸፍናል፡፡
- ጨረታው የሚከፈትበት 11ኛው ቀን የእረፍት ቀን ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በተከታታዩ የስራ ቀን የሚከፈት ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች ሰነድ በሚያስገቡበት ጊዜ ከመስሪያ ቤቱ የተሸጠላቸውን ሰነድ ከዋጋ ማቅረቢያው ጋር መመለስ አለበት፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው የማይመለስ ብር 400 /አራት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ፡፡
አድራሻ፡- ከአየር ጤና ወደ አለም ባንክ በሚወስደው መንገድ ከትሮፒካል ከፍ ብሎ ወረዳ 4 ህንጻ 1ኛ ፎቅ ፋይናንስ ጽ/ቤት
ለበለጠ መረጃ፡- 011-8-33 84 81/ 011-3-69-37-20
የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አስተዳደር የፋይናንስ ጽ/ቤት
