Tender Detail

Tender Details

  • Company Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise (የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት) (ኢኢግልድ)
  • Address በአራዳ ክፍለ ከተማ በወረዳ 02 ፒያሳ ከሊፋ ህንፃ አካባቢ በስተ ሰሜን አቅጣጫ የባቡር ሃዲዱን ተሻግሮ ወደ አራት መንታ በሚወስደው መንገድ ጣልያን ሰፈር (የቀድሞ ጅንአድ መ/ቤት) : አዲስ አበባ ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0111281529
  • Websitehttp://www.eiide.com.et/web/guest/about-us
  • Deadline04 Feb 2026, 12:00 AM
  • magazineአዲስ ዘመን
  • Bid Document Price300.00
  • opening date2026-02-04 00:00:00
  • Categories Health Care, Medical Industry , Health Related Services

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት (ኢኢግልድ) ለሰራተኞች ለአንድ አመት የሚያገለግል የላብራቶሪ የዱቤ ሕክምና አገልግሎት ብቻ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡


ብሔራዊ ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

የግዥ ቁጥር/ኢኢግልድ-002/2018

 

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት (ኢኢግልድ) ለሰራተኞች ለአንድ አመት የሚያገለግል የላብራቶሪ የዱቤ ሕክምና አገልግሎት ብቻ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፡፡

በመሆኑም ማንኛውም ተጫራች በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ማለትም በላብራቶሪ አገልግሎት ብቻ ፍቃድ ያለው፣ የተጨማሪ እሴት ታክስና የግብር ከፋይነት ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ በመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዝርዝር የተመዘገበበት የምስክር ወረቀትና ከገቢዎችና ጉምሩ ባለስልጣን በጨረታ እንዲሳተፍ የተፃፈለትን የድጋፍ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል መሆን ይኖርበታል፡፡

ለዚህ የተዘጋጀውን ዝርዝር የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 300.00 (ሶስት መቶ ብር) በመክፈል ከድርጅቱ ግዥ ቡድን በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ፡፡

ተጫራ ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ኦርጅናል እና ኮፒ ሰነዶች በተለያዩ ፖስታዎች በማድረግ እንዲያቀርቡ እያሳሰብን ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 10 ተከታታይ ቀናት በአየር ላይ ቆይቶ በማግስቱ 11ኛው ቀን 400 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 430 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኢኢግልድ ዋና /ቤት ስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡ ነገር ግን 11ኛው ቀን በዓል ከሆነ ቀጥሎ ባለው የስራ ቀን ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች በጨረታ ለመወዳደር የጨረታ ማስከበሪያ ብር 15,000 (አስራ አምስት ብር ብቻ) የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት (Ethiopian Industrial Inputs Development Enterprise) ስም በሲ.. ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ከጨረታው ቴክኒካል ሰነድ ጋር በማያያዝ ማቅረብ አለባቸው፡፡

ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

አድራሻ : በኢኢግልድ ዋና /ቤት ፒያሳ ከሊፋ ሕንፃ አካባቢ በስተሰሜን አቅጣጫ የባቡር ሃዲዱን ተሻግሮ (የቀድሞ ጅንአድ) አራዳ /ከተማ ወረዳ 2::

ተጨማሪ ማብራሪያ ቢያስፈልግ:- በስልክ ቁጥር 0111-57-24-97 በመደወል ወይም በአካል በመቅረብ ይችላሉ፡፡

የኢትዮጵያ ኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት /ኢኢግልድ/

Save Tender