የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ለሚያስተዳድራቸው ሰራተኞች የህከምና አገልግሎት ለመስጠት እንዲያስችለው የዱቤ ህክምና አገልግሎት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ለሚያስተዳድራቸው ሰራተኞች የህከምና አገልግሎት ለመስጠት እንዲያስችለው የዱቤ ህክምና አገልግሎት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ ተጫራቾች፡-
1. የተጨማሪ አሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ፣ በጨረታ ለመወዳደር የሚያስችል ክሊራንስ፣ ሕጋዊና የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ሰርተፊኬት ያላቸው እና የሙያ ብቃት ማረጋገጫ ያላቸው መሆን አለባቸው።
2. የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00 በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 የሥራ ቀናት ውስጥ በሥራ ሰዓት የፋይናንስ ቢሮ በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ፡፡
3. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 የሥራ ቀናት ውስጥ በጨረታ ሰነዱ ላይ የዕቃዎች ዋጋ ዝርዝር በመሙላትና የጨረታ ማስከበሪያ በማካተት በአገልግሎቱ ዋና መ/ቤት የግገዢ ቡድን ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ እስከ ከጠዋቱ 04:00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ 10,000.00 (አስር ሺ ብር) የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት -Refugees and & Returnees Service በሚል የተዘጋጀ የባንክ የክፍያ ማዘዣ /CPO/ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ ሲፒኦ ቴክኒካል መስፈርት ከያዘ ሰነድ ጋር አብሮ መግባት ይኖርበታል፡፡
5. ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10ኛው የስራ ቀን ከቀኑ 04:00 ሰዓት ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ04:30 ይከፈታል፡፡ /ቅዳሜና እሁድ የመ/ቤቱ የሥራ ቀናት እይደሎም/፡፡
6. ተጫራቾች ሁለት ሰነዶች ማለትም ቴክኒካል ሰነድ በጨረታ ሰነድ ላይ የተካተተውን ቼክሊስት ጨምሮ እና ፋይናንሽያል መስፈርቶች የያዙ ለየብቻ በማሸግ እገልግሎት መስሪያ ቤቱ በሚያዘጋጀው የጨረታ ሳጥኖች ማስገባት ይጠበቅባቸዋል።
7. የጨረታው አሸናፊ ጥሪ በደረሰው በ5 /አምስት/ ቀናት ውስጥ በአገልግሎቱ ዋና መ/ቤት ቀርቦ የሥራ ውል መፈረም አለበት፡፡
8. አሸናፊው ጥሪ በደረሰው በአምስት ቀናት ውስጥ በአገልግሎቱ ዋና መ/ቤት ቀርቦ ውል ካልፈረመ አሸናፊነቱ ተሰርዞ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ለመ/ቤቱ ገቢ ይሆናል፡፡
9. አገልግሎት መስሪያ ቤቱ የተሻለ እማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፈል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ
የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት
የእንቁላል ፋብሪካ አደባባይን ሳይሻገሩ
ክፌደራል ፖሊስ ክበብ ፊት ለፊት
ስልክ ቁጥር 09-97-23-66-31
የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት
