በደ/ኢት/ሥራና ክህሎት ቢሮ አረካ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 በጀት ዓመት በስድስቱ ሎቶች ማለት፡- ሎት1 GMFA,SERVEYING እና BE ሎት2 አውቶሞቲቭ፣ ሎት3 ኤሌክትሮኒክስ እና ኤሌትሪካል መሣሪያዎች ሎት 4 ተገጣጣሚዎች፣ ሎት 5 ቋሚና አላቂ ጽ/መሣሪያ፣ ሎት6 ጋርመንትና ደንብ ልብስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የብሔራዊ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በደ/ኢት/ሥራና ክህሎት ቢሮ አረካ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 በጀት ዓመት በስድስቱ ሎቶች ማለት፡- ሎት 1 GMFA,SERVEYING እና BE ሎት 2 አውቶሞቲቭ፣ ሎት 3 ኤሌክትሮኒክስ እና ኤሌትሪካል መሣሪያዎች ሎት 4 ተገጣጣሚዎች፣ ሎት 5 ቋሚና አላቂ ጽ/መሣሪያ፣ ሎት 6 ጋርመንትና ደንብ ልብስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ በዚሁ መሰረት ተጫራቾች፡-
1. በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው እና የ2018 ዓ.ም ያሳደሰበት ፍቃድ ማቅረብ የሚችል፣ የምዝገባ ምስክር ወረቀት፣የቲን ምዝገባ ሰነድና የተጨማሪ ዕሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆነበትን ማስረጃ ከአቂራቢነት ማስረጃ ጋር ማቅረብ የሚችል
2. የጨረታ ማስከበሪያ በአንድ ጨረታ ሰነድ 5,000.00 (አምስት ሺህ ብር) በሲፒኦ ብቻ የሚያቀርብ፣ ንብረቱን እስከ መስሪያ ቤቱ ድረስ ማቅረብ የሚችል ሆኖ የዕቃውን ጥራት የተቋሙ/ ጥራት ኮሚቴ አጣርቶ ሲረከብና ንብረት ክፍል ገቢ ሲሆን ብቻ ክፍያ ለመጠየቅ ፍቃደኛ የሚሆን
3. የጨረታ ሰነዱ ኮፒ ተደርጎ በኦርጅናልና ኮፒ ላይ ተፈርሞ የድርጅቱን ማህተም በማሳረፍ በፖስታ ታሽጎ ማቅረብ አለበት፤ ድልዝ ስርዝ ካለበት የጨረታ ሰነድ ዋጋ የለውም፤
4. አሸናፊው ተጫራች ያሸነፈበትን ዋጋ በሐምሌ 2017 ዓ.ም ተሻሽለው በወጣው ግዥ አፈጻጸም መመሪያ መሰረት የሚመለስ የውል ማስከበሪያ ገንዘብ በማስያዝ የጨረታ ውጤት ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ 15/አስራ አምስት በሥራ ቀናት ውስጥ ቀርቦ ውል መግባትና በወቅቱ ውል ገብቶ በውል መሰረት ዕቃውን የሚያቀርብ፣ባያቀርብ መ/ቤቱ ለውል ማስከበሪያም ሆነ ለጨረታ ማስከበሪያ በሲፒኦ ያስያዘው ገንዘብ ይወረሳል። ለሚደርስበትም ኪሳራ በህጉና በአዋጁ መሠረት ተጠያቂ ያደርጋል፣ በግዥ አዋጅና መመሪያ መሠረት ለአንደኛ ተጠባባቂ ይሰጣል፡፡
5. ተጫራች ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከታወጀበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 400.00 በመክፈል ሰነድ በመግዛት 15 /አስራ አምስት/ በሥራ ቀናት ውስጥ ለጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ በመክተት በ15ኛ ሥራ ቀን ከቀኑ በ8፡00 ሰአት ታሽጎ በ8፡30 ላይ ይከፈታል፤ ጨረታው ሲከፈት ባለቤት ተወካይ⁄ ያለመገኘት ጨረታውን እያስተጓጉልም።
6. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ከወላይታ ሶዶ ከተማ በስተ-ሰሜን አረካ ከተማ
በስልክ ቁጥር፡- 0922498790-0916684122
በደ/ኢት/ሥራና ክህሎት ቢሮ አረካ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
