የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ሎት 1 የደንብ ልብስ ግዢ እና ሎት 2 የገበያ ጥናት ትንቢያ ግዥ በጨረታ አወዳድሮ ለመፈጸም ይፈልጋል።
ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ የጨረታ
ማስታወቂያ ቁጥር 03//2018
የግዢው አይነት
ሎት 1 የደንብ ልብስ ግዢ
ሎት 2 የገበያ ጥናት ትንቢያ ግዥ
1. በዘርፉ ህጋዊ ፍቃድ ያለውና የ2018 የታደሰ የንግድ የስራ ፍቃድ ያላቸው።
2. ለዕቃ አቅራቢነት ስለመመዝገባቸው እንዲሁም ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው መረጃ ማቅረብ የሚችሉ
3. የጨረታ ማስከበሪያ በእያንዳንዱ ሎት ብር 20,000 /ሃያ ሺህ ብር/ ወይም በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ስም CPO (ጋራንት ቢድ ቦንድ) በማሰራት ማስያዝ የሚችሉ።
4. የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ ከመጨረሻው ቀን በኋላ ለተጨማሪ 90 ቀናት ፀንቶ ይቆያል።
5. ይህ የጨታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
6. ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሃሳባቸውን የአንዱ ዋጋ እና ጠቅላላ ዋጋ ተጨማሪ እሴት ታክስን ያካተተ ዋጋ ስርዝ ድልዝ ሳይኖረው ቢሮው በሰጣችሁ ፎርማት ላይ በመሙላት እና የድርጅታችሁ ማህተም ፊርማና ሙሉ አድራሻችሁን በመግለጽ።
6.1. ፋይናንሽያል አንድ ኦሪጅናል እና እና ፋይናንሽያል አንድ ኮፒ
6.2. ቴክኒካል እና አንድ ኦርጅናል እና ቴክኒካል አንድ ኮፒ በማድረግ በሰም በታሸገ በተለያዩ ፖስታዎች ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
6.3. ለሎት 1 ቢሮ በሚያቀርበው ዝርዝር /ናሙና/ መሠረት ማቅረብ የሚችል
7. ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ከመጀመሪያ ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ከሰኞ ዓርብ ከ2፡30-11 ሰዓት ድረስ የግዥ ዳሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 803 በዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
8. ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣ በ11ኛው ቀን ማለትም የሥራ ቀን ካልሆነ ቀጥሎ ባለው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጐ በዚያኑ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
9. ማንኛውም ተጫራች በሌሎች ተጫራቾች ላይ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት /ማቅረብ/ አይቻልም።
10. ቢሮው ብዛቱን በተመለከተ በጨረታ ሰነዱ ላይ በገለፅነው መሠረት መቀነስና መጨመር የሚቻል መሆኑን እንገልፃለን።
11. ቢሮው የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በመሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር፡- 011 8 12 61 79/ 011 1 70 30 24/ በመደወል መረጃ መጠየቅ ይቻላል።
አድራሻ፡- በአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር ንግድ ቢሮ ውቤ በረሃ 8ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 803
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ
