በአ/ብ/ክ/መ በደቡብ ወሎ ዞን በደሴ ዙሪያ ወረዳ አካባቢና ደን ጥበቃ ጽ/ቤት በ040 (ሃራወበሎ ቀበሌ) የሚገኘውን የለማ የማህበረሰብ ደን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በአ/ብ/ክ/መ በደቡብ ወሎ ዞን በደሴ ዙሪያ ወረዳ አካባቢና ደን ጥበቃ ጽ/ቤት በ040 (ሃራወበሎ ቀበሌ) የሚገኘውን የለማ የማህበረሰብ ደን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
በዚህም መሰረት ማንኛውም ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሞሉ ከሆነ መወዳደር ይቻላል፡፡
1. በአጣና ወይም በጣውላ ንግድ ስራ የተሰማሩ በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው የቫት ተጠቃሚና ግብር አጠናቀው የከፈሉ መሆኑን ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
2. ለግል ፍጆታ ጥቅም ላይ ማዋል የሚፈልጉ መንግስታዊ መ/ቤቶች፣ በከፊል መንግስታዊ ድርጅቶች፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ፣ ማህበራትና ግለሰቦች በጨረታው መሳተፍ ይቻላል፡፡
3. ለጨረታ የቀረበውን ደን ማየት የሚፈልጉ ተጫራቾች ለዚሁ ሲባል በተዘጋጀው የመጫረቻ ሰነድ ላይ በተገለጸው ቦታ ድረስ በመሄድ ጨረታው ለመጀመሪያ ጊዜ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ20 ተከታታይ ቀናት ማየት ይቻላል፡፡
4. የተዘጋጀው የጨረታ ሰነድ የሚገኘው የደሴ ዙሪያ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በመገኘት ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ ብር 300 (ሶስት መቶ ብር) በስራ ቀን ከፍሎ መግዛት ይቻላል።
5. ተጫራቾች የሚጫረቱበትን የደን አይነት ለመግዛት የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ 10% ጨረታ ማስከበሪያ በባንክ ክፍያ ማዘዣ /CPO/ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
6. ተጫራቾች የሚገዙበትን ዋጋ ከስማቸውና ከአድራሻቸው ጋር በተናጠል በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግ በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት በደ/ወሎ ዞን የደሴ ዙሪያ አካ/ደ/ጥ/ ጽ/ቤት የማህበረሰብ ደን ጨረታ ተብሎ በጉልህ ከተጻፈበት በኋላ ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በመቁጠር እስከ 21ኛው ቀን 3፡30 ሰዓት በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
7. ጨረታው በ21ኛው ቀን በ3፡30 ሰዓት ላይ ጨረታው ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በተገኙበት ከጠዋት 4፡00 ላይ ይከፈታል። የመክፈቻ ቀን ቅዳሜ እና እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ ጨረታው በሚቀጥለው የስራ ቀን ይከፈታል፡፡
8. አሸናፊው ተጫራች ጨረታውን ያአሸነፈበትን ዋጋ እና የሮያሊቲ ክፍያ 13% ለመንግስት በአስር ቀን ውስጥ መክፈል ይጠበቅበታል፡፡
9. መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብት በህግ የተጠበቀ ነው።
10. በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ደሴ ዙሪያ ወረዳ አካ/ደ/ጥ/ጽ/ቤት ድረስ በአካል በመገኘት ይጠይቁ፡፡
ስልክ ቁጥር 0914604756/0914737774 ይደውሉ፡፡
የደሴ ዙሪያ ወረዳ አካባቢ ደን ጥበቃ ጽ/ቤት
