የአቃ/ቃ/ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ የመንግስት ግዥ አስተዳደር ቡድን የተሰባበሩ የፈርኒቸር ዕቃዎች እና የህንፃ መሣሪያዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
ያገለገሉ ዕቃዎች ሽያጭ ጨረታ ቁጥር 002/2018
የአቃ/ቃ/ክ/ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ የመንግስት ግዥ አስተዳደር ቡድን የተሰባበሩ የፈርኒቸር ዕቃዎች እና የህንፃ መሣሪያዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
በመሆኑም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን ዝርዝር መስፈርቶች ማሟላት ያለባችሁ መሆኑን እናሳውቃል።
1. በጨረታ በቀረቡ ዕቃዎች ላይ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች በጨረታ ከሚሸጠው ዕቃ ጋር ተዛማጅነት ያለው የታደሰ ንግድ ፍቃድ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት፣ የግብር ከፋይ የምዝገባ ሰርተፊኬት እና የግብር ክሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ።
2. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ አስተዳደር 9ኛ ፎቅ ግዥ ቡድን በመቅረብ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ መን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት በመቅረብ ሰነዱን በመግዛት ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
3. ማንኛውም ተጫራች ለዕቃዎች በአጠቃላይ ያቀረበው ዋጋ 2% (ሁለት በመቶ) የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና CPO ማቅረብ ይኖርበታል። CPO ሲያሰሩ በአቃ/ቃ/ክ/ከ/ዋና/ስ/አስፈጻሚ ፋይናንስ ቡድን ወይም Ak/K/S/C/C/Executive finance team ብለው ያሰሩ።
4. ተጫራቾች ከገዙት ሰነድ ውጪ በሌላ ሰነድ የተሟላ ዋጋ ተቀባይነት የሌለው መሆኑን እንገልፃለን የሚቀርበው ሰነድ ኦርጂናልና ኮፒ ለየራስ በፖስታ በማሸግ ኦርጅናል ላይ ኦርጅናል ኮፒ ላይ ኮፒ ተብሎ ለየራስ ታሽጎ ማቅረብ ይኖርበታል። አሸናፊ ተጫራች ውጤት በደብዳቤ ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ በ3 ቀናት ውስጥ ያሸነፈበትን ገንዘብ ገቢ በማድረግ ዕቃውን በመረከብ ከመጋዘን ማውጣት ያለበት ሲሆን ይህ የማይሆን ከሆነ ጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ዋስትና የሚወረስ ይሆናል። ጨረታው ከ10ኛ ቀን ቀጥሎ ባለው የስራ ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚያው ቀን 3:30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ይሆናል።
ማሳሰቢያ፡- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 0944-31-17-95 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል።
አድራሻ፡- ቃሊቲ መናኸሪያ ፊት ለፊት የሚገኘው የአስተዳደር ህንፃ 9ኛ ፎቅ
የአቃ/ቃ/ክ/ከ/ዋና ስራ አስፈፃሚ የመ/ግ/አስ/ቡድን
