የኢ.ኢ.መ. ጡረተኞች የኮንትራት ሥራዎች ኃላ/የተ/ኅ/ሥራ ማኅበር በኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ኢንተርፕራይዝ ጊቢ ውስጥ የሚገኙ የምግብ ቤት መጠቀሚያ የነበሩ የሚከተሉትን ያገለገሉ እቃዎች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የኢ.ኢ.መ. ጡረተኞች የኮንትራት ሥራዎች ኃላ/የተ/ኅ/ሥራ ማኅበር በኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ኢንተርፕራይዝ ጊቢ ውስጥ የሚገኙ የምግብ ቤት መጠቀሚያ የነበሩ የሚከተሉትን ያገለገሉ እቃዎች ባሉበት ሁኔታ በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
የእቃዎች አይነት |
|
1. |
የዳቦ መጋገሪያ (1) ከ4(አራት) ፓትራ ጋር ፣ ማኮፈሻ (1) |
|
2. |
ያገለገሉ የምግብ ቤት እቃዎች የአልሙኒየም ወንበር፣ የፔፕሲ እና የኮካ ኮላ የአምቦ ውሃ ሳጥኖች ከነጠርሙሱ፣ የቢሮ ወንበሮች፣ ከፋይበር የተሰራ ክብ ጠረጴዛ እና የፕላስቲክ ትሪዎች |
|
3. |
ያገለገሉ የእንጨት እና የብረት ካውንተሮች የተሰባበሩና ያገለገሉ ልዩ ልዩ የምግብ ቤት እቃዎች |
ድርጅታችን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶችን ለሚያሟሉ ተጫራቾች አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
1. የዘመኑ ግብር የተከፈለበት የንግድ ፍቃድ ያለው/ያላት፣
2. ተጫራቾች ለጨረታ ማስረከቢያ የሚጫረቱበትን የመነሻ ዋጋውን 10% በቅድሚያ በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው።
3. ተጫራቾች የመጫረቻውን ቅጽ (ፎርም) ብር 200.00 በመክፈል ከማኅበሩ ጽ/ቤት ቢሮ ማግኘት ይችላሉ።
4. ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በጨረታ ቅጽ (ፎርም) ላይ በትክክል ሞልተው ሕጋዊ ማህተም በማድረግ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ እስከ መጋቢት 30 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ በማህበሩ ጽ/ቤት ቢሮ ማስገባት አለባቸው።
5. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ጨረታው ከሚከፈትበት ቀን ቀደም ብለው ቢያንስ ከ3 ቀን በፊት በማኅበሩ ጽ/ቤት ቢሮ ማስገባት አለባቸው።
6. ጨረታው ሚያዚያ 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ በ 8፡30 ሰዓት በኢትዮጵያ ኤርፖርቶች ኢንተርፕራይዝ ግቢ ውስጥ ተጫራቾች በተገኙበት ይከፈታል።
7. አሸናፊው ተጫራች ተጫርቶ ያሸነፈውን ንብረት በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ማንሳት ይኖርበታል።
8. ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ፤
ስልክ ቁጥር 0911-17-51-49 / 0115-17-82-83 ከ ሰኞ - አርብ ከጠዋቱ 2፡00-11:00 ሰዓት ደውለው መረዳት ይችላሉ።
የማኅበሩ ጽ/ቤት በኢትዮጵያ አየር መንገድ ግቢ ውስጥ የሠራተኞች እና የመንገደኞች ማጓጓዣ አውቶቡስና ላንድ ክሩዘሮች ከሚቆሙበት መነኻሪያ ከስምሪት ቢሮ አጠገብ ይገኛል፡፡
የኢ.አ.መ. ጡረተኞች የኮንትራት ሥራዎች ኃላ/የተ/ኅ/ሥራ ማኅበር
