በየካ ክፍለ ከተማ በወረዳ 10 ት/ት/ጽ/ቤት ኮተቤ የሚገኘው ሳላይሽ ቅድመ አንደኛ 1ኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት አላቂ የቢሮ ዕቃዎች፤ አላቂ የህክምና ዕቃ፤ አላቂ የፅዳት ዕቃ እና ልዩ ልዩ እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በየካ ክፍለ ከተማ በወረዳ 10 ት/ት/ጽ/ቤት ኮተቤ የሚገኘው ሳላይሽ ቅድመ አንደኛ 1ኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት አላቂ የቢሮ ዕቃዎች፤ አላቂ የህክምና ዕቃ፤ አላቂ የፅዳት ዕቃ እና ልዩ ልዩ እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ግዥ ቢሮ ማግኘት ይችላሉ።
ተጫራቾች የጨረታ ማስከበርያ ተመላሽ የሚሆን ብር ለቢሮ ዕቃ ብር 5,000.00(አምስት ሺህ ብር)፣ ለህክምና ዕቃ ብር 7,500.00(ሰባት ሺህ አምስት መቶ ብር)፣ ለፅዳት ዕቃ 1,000.00 (አንድ ሺህ ብር)፣ ልዩ ልዩ 2,500 (ሁለት ሺህ አምስት መቶ ብር) በተረጋገጠ (CPO) ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
በመሆኑም፡-
- ተጫራቾች የዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው።
- የገንዘብ ሚኒስቴር የምዝገባ ምስክር ወረቀት የቫት ተመዝጋቢና የታከስ ከፋይነት ማስረጃ ማቅረብ የሚችል። ቲን ነምበር ያላቸው
- ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 300.00(ሶስት መቶ ብር) በመክፈል ከረዳት ፋይናንስ ቢሮ ቁጥር 10 ማግኘት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ ቫትን አካቶ መሆን አለበት።
- ከጨረታ ኤጀንሲ የአቅራቢነት ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ግብር የከፈሉበት ክሊራንስ ማያያዝ አለባቸው።
- ተጫራቾች የሚያቀርቡበትን ዋጋ ዝርዝር በያዘው በእያንዳንዱ ሰነድ ላይ ማህተምና ፊርማ ማድረግ አለባቸው።
- ተጫራቾች መወዳደርያ ዋጋቸውን የሚያቀርቡት በተሸጠላቸው ሰነድ ላይ ብቻ መሆን አለበት።
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ሰነድ እና ከላይ የተዘረዘሩትን ማስረጃ አያይዘው በአንድ ፖስታ አሽገው ማህተምና የድርጅታቸውን ስም በመጻፍ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 11፡30 ሰዓት ድረስ ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን በአስራ አንደኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ላይ የጨረታ ሳጥኑ ታሽጎ 4፡30 ይከፈታል፡፡ አስራ አንደኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቀጣይ የስራ ቀን 4፡00 ሰዓት ላይ የጨረታ ሳጥኑ ታሽጎ 4፡30 ሰዓት ይከፈታል።
- አሸናፊው እንደታወቀ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበርያ ዋስትና በተረጋገጠ (CPO) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች በሌላ ዋጋ ላይ ተንተርሰው ማቅረብ አይችሉም።
- ተጫራቾች ሳምፕል ለሚቀርብባቸው ዕቃዎች ማቅረብ አለባቸው።
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ኮተቤ 32 ቁጥር አውቶቢስ ማዞርያ ወደ ሃና ቤተክርስቲያን መውጫ መንገድ በስተግራ ኮብልእስቶን መንገድ 800 ሜትር ገባ ብሎ ነው።
ስልክ ቁጥር 0996 038 893
በየካ ክፍለ ከተማ ት/ት/ጽ/ቤት የሳላይሽ ቅድመ አንደኛ፣ 1ኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት
