በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን የወራቤ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት ለማዘጋጃ ቤት አገልግሎት የሚውል ኦራል የእሳት አደጋ መኪና ጎማ በመስከ ፍቃድ ያላቸውን ድርጅቶችን በጨረታ አወደድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን የወራቤ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት ለማዘጋጃ ቤት አገልግሎት የሚውል ኦራል የእሳት አደጋ መኪና ጎማ በመስከ ፍቃድ ያላቸውን ድርጅቶችን በጨረታ አወደድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለሆነም
· በመስኩ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸው
· የንግድ ምዝገባ ምስክር ያላቸው
· ቲን ነምበር ያላቸው
· የዘመኑን ግብር አጠናቀው የከፈሉ
የተጨማሪ እሴት ታከስ የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የምትችሉ በመንግስት ግዢ ለመሳተፍ የአቅራቢነት ሰርተፍኬት ማቅረብ የምትችሉ የጨረታ ዋስትና 50,000 በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ የሚችሉ ተጫራቾች ሰነዱን ከወራቤ ከተማ አስተዳደርፋይናንስ ጽ/ቤት በመምጣት የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 500 /አምስት መቶ ብር/ብቻ በመክፈል መግዛት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን የጨረታ ሰነዱን አንድ ኦርጅናልና ሁለት ፎቶ ኮፒ ለየብቻ በታሸገ ፖስታ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከታተመበት ዕለት ጀምሮ ባሉት 10 አስር/ ተከታታይ የስራ ቀናት በኋላ ባለው የስራ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ በጽ/ቤቱ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታ ሳጥኑ በዚሁ እለት ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ ከጠዋቱ 4:30 መገኘት በሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
ማሳሰቢያ፡-
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- የተሞላው ዋጋ መግለጫ ካልተሰጠበት ከነቫት ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
ለበለጠ መረጃ 0467710211 ይደውሉ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የስልጤ ዞን የወራቤ ከተማ አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት
