የአ/ምንጭ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ለድርጅቱ አገልግሎት የሚሰጡ ከታች በምድባቸው በዝርዝር የተገለጹትን ዕቃ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የአ/ምንጭ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት ለድርጅቱ አገልግሎት የሚሰጡ ከታች በምድባቸው በዝርዝር የተገለጹትን ዕቃ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚህም መሰረት፡-
1ኛ ሎት /ምድብ አንድ/ የደንብ ልብስ
ተጫራቾች ሟሟላት ያለባቸው፡-
1. ከላይ በተጠቀሰው ዕቃ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያለውና የዘመኑን የመንግስት ግብር የከፈለ እንዲሁም በዘርፉ በቀጥታ ተሳታፊ መሆኑን የሚገልፅ ማስረጃ፡፡
2. ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር የደንብ ልብስ አቅራቢ ውሰጥ የተመዘገቡ ስለመሆናቸው የሚገልፅ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችልና የተጨማሪ እሴት ታክሰ ተመዝጋቢ መሆናቸውንና የግብር ከፍይነት መለያ ቁጥር /TIN/ መኖሩን የሚገልጽ ማስረጃ፡፡
3. በሚወዳደሩት የደንብ ልብስ ዓይነቶች ለእያንዳንዱ ልብስ ዓይነት ለውድድር ሲመጡ በየአይነታቸው አንዳንድ ሳምፕል ማቅረብ የሚችል እንዲሁም ተወዳድሮ ሲያሸንፍ ያሸነፋቸውን የደንብ ልብሶችን በራሱ ትራንስፖርት እሰከ ድርጅቱ እስቶር ድረስ በማቅረብ የጫኝና አውራጅ ችሎ ማስረከብ የሚችል፡፡
4. በሚወዳደሩት የደንብ ልብስ ዓይነት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከተፈቀደላቸው ከታወቁ ባንኮች ብር 50,000 /ሀምሳ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ CPO ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ከጨረታ ዶክመንት ጋር ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
5. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ ከፍሎ ከድርጅቱ በመውሰድ በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ /ፖስታ/ ቴክኒካል ዶክመንት ኦርጅናል ለብቻ ቴክኒካል ዶክመንት ኮፒ ለብቻ እንዲሁም ፋይናንሻል ዶከመንት ኦርጅናል ለብቻ ፋይናንሻል ዶክመንት ኮፒ ለብቻ አሽጎ ለጨረታ በተዘጋጀ ሳጥን ውሰጥ በማስገባት መወዳደር የሚችሉ ሲሆን ጨረታው በአርባ ምንጭ ከተማ ውሃና ፍሳሸ አገልግሎት ድርጅት ግቢ በ16ኛው ቀን ተጫራቾች /ህጋዊ ተወካዮቻቸው በተገኙበት በ8፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ8፡30 ላይ የሚከፈት ይሆናል። ሆኖም የጨረታ መዝጊያና መክፈቻ ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይንም የበዓላት ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን መዝግያና መክፈቻ ይሆናል፡፡
6. በሌላ ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ ተቀባይነት የለውም፡፡
7. መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ የስልከ ቁጥር 0468810369/0468812049 መደወል ይቻላል።
የአርባ ምንጭ ከተማ ውሃና ፍሳሽ አገልግሎት ድርጅት
