ድርጅታችን በላይአብ ኬብል አምራች ኃ/የተ/የግ/ማ የተለያዩ ተረፈ ምረቶችን ከታች በዝርዝር የቀረቡትን ባሉበት ቦታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
ድርጅታችን በላይአብ ኬብል አምራች ኃ/የተ/የግ/ማ የተለያዩ ተረፈ ምረቶችን ከታች በዝርዝር የቀረቡትን ባሉበት ቦታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
የዕቃው ዓይነት |
መለኪያ |
ብዛት |
|
1 |
የመዳብ ሽቦ ስክራፕ (Copper Scrap) |
በኪ.ግ |
2,652.1 |
|
2 |
የአሉሚኒየም ሽቦ ስክራፕ (Aluminum Scrap) |
በኪ.ግ |
1,646.00 |
1. ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የሥራ ቀናቶች በድርጅቱ ዋና መ/ቤት አዲስ አበባ በመቅረብ መግዛት ይኖርባቸዋል፡፡
2. ተጫራቾች ዕቃውን ለማየት ዘወትር ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ባሉት የሥራ ሰዓት በድርጅቱ ፋብሪካ አዳማ ወንጂ ማዞሪያ ቀበሌ 09 በአካል በመገኘት መመልከት ይችላሉ፡፡
3. ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው የሥራ ቀን እና የጨረታ ሳጥኑ እስከሚታሸግበት 16ኛው ቀን እስከ 8፡00 ሰዓት ለዚሁ ተግባርበተዘጋጀው ሳጥን በድርጅቱ ዋና መ/ቤት አዲስ አበባ ን/ስ/ላ/ክ/ከተማ ለቡ ኢንዱስትሪ መንደር በአካል በመቅረብ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው በዚሁ ዕለት ከቀኑ 8፡30 ተጫራቾችና ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
4. ተጫራቾች የሚያቀርቡትን ዋጋ 2% (ሁለት በመቶ) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ በድርጅቱ ስም በማሠራት ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
5. የጨረታ ማስከበሪያው ዋስትና ለአሸናፊዎች ሙሉ ክፍያውን እንደከፈሉና ማስረጃ እንዳቀረቡ የሚለቀቅ ሲሆን ለተሸናፊዎች ግን የጨረታ ውጤቱ እንደፀደቀ ይሆናል።
6. አሸናፊ ተጫራች ከድርጅቱ ጋር የሽያጭ ውል ስምምነት ይፈራረማል ከተፈራረመ በኋላ የሚጠበቅበትን ክፍያ በማጠናቀቅ ዕቃውን ይረከባል፡፡
7. ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
8. ስለ ጨረታው ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 09125032/0939554606 ማብራሪያ ማግኘት ይችላሉ።
በላይአብ ኬብል አምራች ኃ/የተ/ግ/ማ
