ሜልባ ፕሪንቲንግ፣ ፐብሊሺንግና ፓኬጂንግ አ.ማ በብሄራዊ ግልጽ ጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለህትመት አገልግሎት የሚውል ውድፍሪ ወረቀት ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡ ሜልባ/ብ/ግ/ጨ/010/2018
ሜልባ ፕሪንቲንግ፣ ፐብሊሺንግና ፓኬጂንግ አ.ማ በብሄራዊ ግልጽ ጨረታ ተጫራቾችን አወዳድሮ ለህትመት አገልግሎት የሚውል ውድፍሪ ወረቀት ለመግዛት ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
የእቃዉ ዓይነት |
መለኪያ |
ብዛት |
የጨረታ ማስያዣ መጠን |
የጨረታ መዝጊያ ቀንና ሰዓት |
የጨረታ መክፈቻ ቀንና ሰዓት |
|
1 |
Woodfree Paper 80 GSM 84CM |
ቶን |
450 |
የአጠቃላይ ኮንትራት ዋጋ 1% ግን ከ500,000.00 ብር ያልበለጠ |
01/10/2018 ከቀኑ 9፡00 |
01/10/2018 ከቀኑ 9፡10 |
በዚህ መሰረት፣
1. በጨረታው ላይ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ማንኛውም ተጫራቾች አግባብነት ያለው የ 2018 የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት፣ የግብር ከፋይ ሰርተፊኬት፣ በጨረታው መወዳደር የሚያስችል የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ታክስ ክሊራንስ እንዲሁም የአቅራቢዎች ምዝገባ (suppliers list) ላይ መመዝገባቸውን የሚገልጽ ሰርተፍኬት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
2. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 300.00 /ሶስት መቶ ብር/ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ገቢ በማድረግ ገቢ ያደረጉበትን ዋና ደረሰኝ ይዞ በመቅረብ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከድርጅቱ መ/ቤት የግዥ ዳይሬክቶሬት 2ኛ ፎቅ መውሰድ ይችላሉ።
3. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ (CPO) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሠረተ የባንክ ዋስትና (Unconditional Bank Guarantee) ከመጫረቻ ሰነዳቸዉ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ከባንክ የሚቀርበው የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለ90 ቀናት ፀንቶ የሚቆይ መሆን ይኖርበታል።
4. ማንኛውም ተጫራች የመጫረቻ ሰነዱን ቴክኒካልና ፋይናንሻል ዋናዉንና ቅጅ በተለያየ ፖስታ በማሸግና ሁሉንም በአንድ ላይ በሚይዝ በሰም በታሸገ ፖስታ ከላይ በሰንጠረዡ የጨረታ መዝጊያ ተብሎ እስከ ተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ድረስ በአክሲዮን ማህበሩ ዋና መ/ቤት 2ኛ ህንጻ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
5. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሚገኙበት ከላይ በሰንጠረዡ የጨረታ መክፈቻ ተብሎ በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት በድርጅቱ ዋና መ/ቤት ይከፈታል።
6. አክሲዮን መህበሩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ሜልባ ፕሪንቲንግ ፐብሊሺንግና ፓኬጂንግ አ.ማ
ቦሌ ሚካኤል ኢጃ ዴቬሎፐር ህንጻ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎ አጠገብ
ለተጨማሪ ማብራሪያ ስ.ቁ.+251 011 8 55 00 83-/ +251 911 96 87 80
ፊንፊኔ / ኢትዮጵያ
ሜልባ ፕሪንቲንግ፣ ፐብሊሺንግና ፓኬጅንግ አ.ማ
