አዋሽ ባንክ አ.ማ በፅህፈት ሥራ ላይ ላልተሰማሩ የባንኩ ሰራተኞች የደንብ ልብስ ማሰፋት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር AB-36/2025/26.
1. አዋሽ ባንክ አ.ማ በፅህፈት ሥራ ላይ ላልተሰማሩ የባንኩ ሰራተኞች የደንብ ልብስ ማሰፋት ይፈልጋል።
2. በዚሁ መሠረት በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ በመስኩ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው በተጨማሪ እሴት ታክስ መመዝገባቸውን የሚገልፅ ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ እና የመንግስት ግብር ከፍለው ያጠናቀቁ መሆን አለባቸው።
|
ተ/ቁ |
መግለጫ |
መለኪያ |
ብዛት |
ምርመራ |
|
1 |
የሴት ኮት እና ሱሪ ሙሉ ልብስ ስፌት በሙሉ ገበር |
ሙሉ ልብስ |
324 444 |
የገበር ጨርቅ ከተጫራች ይሆናል |
|
2 |
የሴት ኮት እና ጉርድ ቀሚስ ስፌት በሙሉ ገበር |
|||
|
3 |
የወንድ ሙሉ ልብስ ስፌት ኮት እና ሱሪ በሙሉ ገበር |
3. በተጫራቾች የሚቀርበው የስፌት ዋጋ በደንብ ሊነበብ በሚችል የእጅ ፅሑፍ ወይም በኮምፒዩተር ተፅፎ መቅረብ ይኖርበታል፡፡ ስርዝ ድልዝ ካለው ከጨረታ ውጪ ይሆናል።
4. ተጫራቾች የተዘጋጀውን ሰነድ ከግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በስራ ሰዓት ከጠዋቱ 2፡00 እስከ 6:00 ሠዓት ከሰዓት ከ 7፡00 እስከ 11፡00 ሰዓት ድረስ በአዋሽ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 01540000544500 በየትኛውም የባንኩ ቅርንጫፍ ብር 500.00 (አምስት መቶ) ገቢ በማድረግ አዋሽ ባንክ ዋና መ/ቤት ህንፃ 12ኛ ፎቅ በሚገኘው የባንኩ ግዥ ዋና ክፍል ቢሮ በአካል ቀርቦ መውሰድ ይችላሉ።
5. በተጫራቾች የሚቀርበው ዋጋ የእጅ እና የገበር ዋጋን ያካተተ መሆን አለበት፡፡
6. ተጫራቾች የሚያስገቧቸውን ኦርጂናል እና ኮፒ የቴክኒካል እና የዋጋ ሠነዶች ለየብቻ (ለየቅል) በታሸገ ኤንቨሎፕ በዕለቱ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ድረስ አዋሽ ባንከ ዋና መ/ቤት ህንፃ 12ኛ ፎቅ በሚገኘው የባንኩ ግዥ ዋና ክፍል ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
7. ጨረታው በእለቱ ግንቦት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከረፋዱ 4፡30 ሰዓት ከላይ በተራ ቁጥር 4 ላይ በተጠቀሰው አድራሻ ይከፈታል፡፡
8. ከላይ ከተራ ቁጥር 1-6 ያሉትን መስፈርት ያላሟሉ ተጫራቾች ከጨረታ ውጪ ይሆናሉ፡፡
9. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0115-57-11-07 ወይም 0115-57-00-84 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
10. ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አዋሽ ባንክ አ.ማ
