ብርሃን ባንክ በ2018 በጀት ዓመት ለሰራተኛች አገልግሎት የሚውል ጃኬት ግዥ ለማከናወን በዘርፉ የተሰማሩ ተጫራቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
በድጋሚ የወጣ የጃኬት ግዥ ጨረታ
አገር አቀፍ የግልጽ ጨረታ
የጨረታ ቁጥር ብ/ባ/ግጨ/ደል/2025/26/23
- ብርሃን ባንክ በ2018 በጀት ዓመት ለሰራተኛች አገልግሎት የሚውል ጃኬት ግዥ ለማከናወን በዘርፉ የተሰማሩ ተጫራቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
- ተጫራቶች በጨረታው ለመሳተፍ የብር 100,000.00 (ብር አንድ መቶ ሺ) የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ ማዘዣ (CPO) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና (Bank Guarantee) መልክ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቶች ለዘመኑ የታደሰ ንግድ ፍቃድ፣የተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይ የምስክር ወረቀት እና የታክስን ከፋይነት የምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው ፡፡
- ተጫራቶች የማይመለስ ብር 345.00 (ብር ሦስት መቶ አርባ አምስት) በማንኛውም የብርሃን ባንክ አ.ማ ቅርንጫፍ ክፍያ ፈጽመው ደረሰኙን በማቅረብ ከባንኩ ዋና መ/ቤት ከሚገኝበት ቦሌ ድልድይ ወመሳድኮ ህንጻ 2ኛ ፎቅ ከሰፕላይ ቼን እና ውል አስተዳደር መምሪያ ቢሮ የጨረታውን ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቶች የጨረታ ሰነዱን ህጋዊ ሰነዶችና የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ሰነድ በአንድ ፖስታ እና የዋጋ ሰነድ በሁለተኛ ፖስታ በዋና እና በኮፒ ማቅረብ ሲኖርባቸው ለሚሳተፉበት ጃኬት ናሙና ማቅረብ ግዴታ አለባቸው ፡፡
- ተጫራቶች የመጫረቻ ሰነዳቸውን እስከ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ በባንኩ ዋና መ/ቤት በሚገኝው ቦሌ ድልድይ ወመሳኮድ ህንጻ 2ኛ ፎቅ ከሰፕላይ ቼን እና ውል አስተዳደር መምሪያ ቢሮ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታው ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡30 ተጫራቶች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከላይ በተገለጸው ቢሮ ይከፈታል፡፡
- ባንኩ የተሻለ ዘዴ ካገኝ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብት አለው፡፡
ብርሃን ባንክ አ.ማ
ከሰፕላይ ቼን እና ውል አስተዳደር መምሪያ
ስልክ ቁጥር0116632097/0116507422
