የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከታች ቀጥሎ በሎት አንድ እና በሎት ሁሉት የተዘረዘሩትን ዴስክ ቶፕ ኮምፒውተር እና የደንብ ልብስ እቃዎችን ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ከታች ቀጥሎ በሎት አንድ እና በሎት ሁሉት የተዘረዘሩትን ዴስክ ቶፕ ኮምፒውተር እና የደንብ ልብስ እቃዎችን ለመግዛት በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ የጨረታ ቁጥር ኢግ.ሥ.ኮ./ብግጨ/17/2018
|
ተ.ቁ |
የሎት ቁጥር |
የጨረታ አይነት |
የጨረታ ሰነድ መሸጫ ዋጋ (የማይመለስ) በብር |
ማስከበሪያ በብር |
የጨረታ መዝጊያና መክፈቻ ቀንና ሰዓት |
||
|
የመዝጊያ ቀን |
የመዝጊያ ሰዓት |
የመክፈቻ ሰዓት |
|||||
|
1 |
ሎት አንድ |
ዴስክ ቶፕ ኮምፒውተር ግዥ |
200 |
100ሺህ |
ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም |
4፡00 |
4፡30 |
|
2 |
ሎት ሁለት |
የአደጋ መከላከያ እና የደንብ ልብስ ግዥ |
200 |
100ሺህ |
ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም |
8፡00 |
8፡30 |
የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከላይ በሠንጠረዥ ውስጥ በዝርዝር እንድተገለፀው እና ከጨረታ ሰነዱ ጋር በተያያዘው ቴከኒካል መስፈርት መሰረት ተጫራቾችን አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች፤
1. በዘርፍ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ፤ ቲን፤ ቫት፤ በEGP/PPA የአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ ስለመመዝገባችሁ እንዲሁም ከገቢዎች ሚ/ር ክሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ ተጫራቾች ዘወትር በሥራ ሰዓት ሳሪስ አቦ ፋፋ የምግብ አማ አጠገብ የቀድሞው እርሻ መሣሪያዎችና ቴክኒክ አገልግሎት አ.ማ. ግቢ የኮርፖሬሽኑ ዋና መ/ቤት ግዥ ክፍል ቀርበው የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ከላይ በእያንዳንዱ ሎት በተገለፀው ብር መሰረት በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ፡፡
2. ተጫራቾች የሚሞሉት ዋጋ በግልፅ የሚታይና ስርዝ ድልዝ የሌለበት መሆን ይኖርበታል፡፡
3. ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና (ለ60 ቀናት የሚቆይ) ማስከበሪያ ከላይ በተገለፀው መሰረት በሰ.ፒ.ኦ. ወይም በባንክ ጋራንቲ (unconditional) ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡ የጨረታ ዋስትናው ለብቻው በአንድ ፖስታ ውስጥ ተደርጎ ከኦርጂናል ቴክኒካል ሰነድ ጋር ተያይዞ መቅረብ ይኖርበታል፡፡ የጨረታው ዋጋ ለ60 ቀናት የጸና ይሆናል፡፡
4. ተጫራቾች ከጨረታ ሰነዱ ጋር ተያይዞ በቀረበው ዶክመንት መሰረት እያንዳንዱ ሎት- 1 እና በሎት-2 ለየብቻ በማድረግ ቴክኒካል ኦርጂናልና ኮፒ እንዲሁም ፋይናንሽያል በተለያዩ ፖስታ በማድረግ ፋይናንሽያል ሰነዱ ዋና እና ኮፒ በመለየት በታሸገ ኤንቨሎፕ አድርገው በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
5. ጨረታው የሚዘጋበት እና የሚከፈትበት ቀን እና ሰዓት ከላይ በሠንጠረዥ ውስጥ በተገለፀው መሰረት ሁኖ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኮርፖሬሽኑ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የቴክኒካል ጨረታ ሰነድ የመክፈቻ ስነሥርዓት ይከናወናል፡፡
6. ኮርፖሬሽኑ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ፡- የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን
+251911984467/+251910567578
አዲስ አበባ
የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን
