የኢትዮጵይ ልማት ባንክ በአዋጅ ቁጥር 97/90፣ 216/92 እና 1147/2011 መሰረት በብድር ዕዳ ምክንያት የተረከበውን አዚህ በታች በሰንጠረዡ የተዘረዘረውን ንብረት በድርድር ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵይ ልማት ባንክ በአዋጅ ቁጥር 97/90፣ 216/92 እና 1147/2011 መሰረት በብድር ዕዳ ምክንያት የተረከበውን አዚህ በታች በሰንጠረዡ የተዘረዘረውን ንብረት በድርድር ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
የቀድሞ ተበዳሪው/ የመያዣ ሰጪው ስም |
የንብረቶቹ ዓይነት በጥቅል |
የማሽነሪ ስም |
የጨረታ መነሻ ዋጋ (በብር) |
ንብረቶቹ የሚገኙበት ቦታ |
የጨረታ ሁኔታ |
ጨረታው የሚካሄድበት ቀንና ሰዓት |
|
1 |
ኤምቴኬ ኢንጅነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማ |
ማሽነሪዎች እና እኩፕመንት |
የእንጨት ስራ ማሽነሪ (Surface planner mic, Circular saw m/c, Edge bending mic. Copy lathe m/c, Combined surface or thickness planner m/c |
ብር 6,185,295.80 (ስድስት ሚሊዮን አንድ መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ ሁለት መቶ ዘጠና አምስት ብር ከሰማንያ ሳንቲም) |
ገላን ከተማ ኤም ቴኬ ኢንጅነሪንግ ፋብሪካ ቅጥር ግቢ ውስጥ |
ድርድር |
ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00-6፡00 ሰዓት |
|
2 |
የብረት ሥራ ማሽነሪ (lathe m/c, universal milling m/c, press brake m/c, scroll bending m/c, hydraulic bending m/c, motor unit,tube drilling m/c etc)
|
ብር 26,174,644.44 (ሃያ ስድስት ሚሊዮን አንድ መቶ ሰባ አራት ሺህ ስድስት መቶ አርባ አራት ብር ከአርባ አራት ሳንቲም) |
|||||
|
3 |
ዎርክ ሾፕ ዩትልትስ (Air compressor, hand pallet, liquid thank) |
ብር 523,134 (አምስት መቶ ሃያ ሦስት ሺህ አንድ መቶ ሰላሳ አራት ብር) |
|||||
|
4 |
ስቶን ዎርክ ዩትልትስ (Special shaped stone polishing, multi-blade bridge block cutter m/c stone surface thickness calibrating m/c etc) |
ብር 1,701,600.00 (አንድ ሚሊዮን ሰባት መቶ አንድ ሺህ ስድስት መቶ ብር ) |
|||||
|
5 |
የቢሮ ዕቃዎች |
ብር 650,051 (ስድስት መቶ ሃምሳ ሺህ ሃምሳ አንድ ብር) |
|||||
|
6 |
ጀነሬተር |
ብር 697,151 (ስድስት መቶ ዘጠና ሰባት ሺህ አንድ መቶ ሃምሳ አንድ ብር) |
|||||
|
7 |
ካርጎ ትራክ |
3-01-77197 አአ |
ብር 410,562.00 (አራት መቶ አስር ሺህ አምስት መቶ ስልሳ ሁለት ብር ) |
||||
ማሳሰቢያ፡-
1. ተጫራቾች የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በመግዛት ንብረቶቹን የሚገዙበትን ዋጋ፤ ስምና አድራሻቸውን በፎርማቱ ላይ በመጥቀስ በባንኩ ዋና መ/ቤት ሁስተኛ ታወር ምድር ቤት ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣ ከሦስተኛው ቀን ጀምሮ እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡50 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይችላሉ:: ሐምሌ 30 ቀን 2018 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ላይ ይከፈታል።
2. ተጫራቾች የሚጫረቱትን ንብረት መነሻ ዋጋ 10 በመቶ በባንክ ክፍያ ማዘዣ /ሲ.ፒ.አ/ ብቻ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ::
3. አሸናፊ የሆነው ተጫራች ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ በ15 /በአስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት ውስጥ አጠቃሎ መክፈል ይኖርበታል፤ በዚህ ጊዜ ውስጥ ካልከፈለ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ጨረታው ይሰረዛል::
4. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሰንጠረዡ በተመለከተው ቀንና ሰዓት በባንኩ ዋናው መ/ቤት ታወር ሁለት 5ኛ ፎቅ በሚገኘው መሰብሰቢያ አዳራሽ ይካሄዳል:: ህጋዊ ሰውነት ያላቸው ወክሎ በጨረታው ለመሳተፍ የሚቀርብ ሰው የማህበሩ መመስረቻ ጽሁፍ/መተዳደሪያ ደንብ ከእነ ማሻሻያዎቹ (ካለ)፤ የንግድ ምዝገባ፣ የንግድ ፈቃድ፣ ሌሎች አስፈላጊ ማስረጃዎችን እና የተረጋገጠ የውክልና ስልጣን ሰነዶችን ይዞ መቅረብ ይኖርበታል::
5. 15% የተጨማሪ እሴት ታክስና ሌሎች ገዢ እንዲከፍላቸው በሕግ የተወሰኑ ክፍያዎችን የስም ማዛወሪያ ክፍያን ጨምሮ ገዢው ይከፍላል::
6. አንዳንድ ንብረቶች የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ ያልተከፈለባቸው ስለሆነ ገዢው የቀረጥ ነጻ መብት ሊኖረው አሊያም የሚፈለገውን ቀረጥ/ታክስ ለመንግስት ለመክፈል ይገደዳል::
7. ባንኩ ለሽያጭ የቀረቡትን ንብረቶች የሚሸጠው ሙሉ በሙሉ በጥሬ ገንዘብ ይሆናል::
8. የንብረቱ ስሙ ንብረት ለገዥው እንዲዞር ባንኩ ለሚመለከተው መንግስታዊ አካል ደብዳቤ ይጽፋል:: ገዥው ጉዳዩን ተከታትሎ ያስፈጽማል::
9. የጨረታ አሸናፊው ማሽነሪዎችን ለመንቀልና ለማጓጓዝ የሚያስፈልግ ወጪ በራሱ ይሸፍናል::
10. ንብረቶቹ ለጨረታ የቀረቡት በየተራ ቁጥሩ በተናጠል ነው::
11. በጨረታው ዝርዝር እና ተጨማሪ መረጃን ለማግኘት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዋና መ/ቤት ታወር ሁለት ሦስተኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የአንጎይንግ ኮንሰርን ፕሮጀክትስ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 011-524-53-73/011-524-42-69 ደውሎ ማግኘት ይቻላል::
12. ተጫራቾች አስቀድሞ ከባንኩ ጋር ቀጠሮ በመያዝ ንብረቶቹን መጎብኘት ይችላሉ::
13. ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
የኢትዮጵያ ልማት ባንክ
