የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ በ2018 የበጀት ዓ.ም ለሰልጣኞች ምግብ አገልግሎት የሚውል የስንዴ ዱቄት የስጋ በሬ፣ የምግብ ጥራጥሬ ዕቃዎች፣ አትክልቶች፣ ቅመማቅመሞች፣ የማገዶ እንጨት፣ የተለያዩየ የፅዳት እና የፅህፈት ዕቃዎችን በግልዕ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የግዥ ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር ኦፖኮ/01/2019
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ በ2018 የበጀት ዓ.ም ለሰልጣኞች ምግብ አገልግሎት የሚውል
የስንዴ ዱቄት የስጋ በሬ፣ የምግብ ጥራጥሬ ዕቃዎች፣ አትክልቶች፣ ቅመማቅመሞች፣ የማገዶ እንጨት፣ የተለያዩየ የፅዳት እና የፅህፈት ዕቃዎችን በግልዕ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል። በዚህ መሰረት በጨረታው ለመሳተፍ ለምትፈልጉ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸው ተጫራቾች ከኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ አዳማ የጨረታውን ሰነድ በመግዛት ጨረታው ላይ መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ለመወዳደር የምትፈልጉ ድርጅቶች ነጋዴዎች አትራቢዎች፡-
1. በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፍቃድ የ2018/2019 ያለውና ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።
2. የሥራ ግብር ከፋይ መሆኑን የሚገልፅ የቲን ቁጥር መረጃ ማቅረብ የሚችል።
3. ተጫራቾች በአቅራቢዎች ስም ዝርዝር (Supply List) ውስጥ መመዝገባቸውን የሚገልፅ መረጃ ማቅረብ የሚች።
4. ግብር መክፈላቸውን የሚገልዕ መረጃ (ኪሊራንስ) ማቅረብ የሚችል።
5. የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT 15%) ተመዝጋቢ መሆኑን የሚገልፅ መረጃ ማቅረብ የሚችል።
6. ማንኛውም ተጫራች ለውድድር ያቀረቡትን ጠቅላላ ዋጋ የጨረታ ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ (CPO) 2% ከጨረታ ሰነድ ጋር በፖስታ አሽጎ ማቅረብ አለባቸው።
7. የጨረታ ሰነዱ የተዘጋጀው በኦሮሚኛ ቋንቋ ስለሆነ ተጫራቾች የማይመለስ ብር 200 (ሁለት መቶ) ብር በመክፈል ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከሰኞ እስከ ቅዳሜ የጨረታ ሰነዱን በኮሌጅ ቅጥር ጊቢ ፋይናንስ ቢሮ በማቅረብ መውሰድ/መግዛት ይችላሉ።
8. ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋናውንና ኮፒውን በተናጥል በፖስታ አሽገው ማቅረብ አለባቸው።
9. የጨረታው ሰነድ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እሁድን ሳይጨምር ለ15 (አስራ አምስት) ተከታታይ ቀናት አየር ላይ ቆይተው በ16ኛው ቀን እስከ 5፡30 ሰዓት ተሸጦ የጨረታው ሰነድ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ገብቶ በዚሁ ዕለት ሳጥኑ ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ላይ ታሽጎ በዚሁ ቀን ከሰዓት ቦዋላ በ8 00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወክሎቻቸው በተገኙበት በይፋ በኮሌጁ አዳራሽ ውስጥ ይከፈታል።
10.ኮሎጁ በሚገዛው ማንኛውም ዕቃ ላይ 50% የመቀነስና የመጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው።
11.ኮሌጁ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
12.አጠቀላይ ዝርዝር መግለጫ ከጨረታ ሰነድ ማግኘት ይችላሉ።
13.ለበለጠ መረጃ በስ/ቁጥር 09 42 41 06 95፣ 09 13 37 94 64 እና 09 23 07 27 06 ደውሎ መጠየቅ ይችላሉ።
የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሌጅ
