አዋሽ ባንክ አ.ማ. በጽሕፈት ሥራ ላይ ላልተሰማሩ የባንኩ ሠራተኞች የደንብ ልብስ ማሰፋት ይፈልጋል።
AwashBank
የጨረታ ማስታወቂያ .
የጨረታ ቁጥር፡ RE-AB/002/2026-27
1. አዋሽ ባንክ አ.ማ. በጽሕፈት ሥራ ላይ ላልተሰማሩ የባንኩ ሠራተኞች የደንብ ልብስ ማሰፋት ይፈልጋል።
2. በዚሁ መሠረት በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ በመስኩ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው፣ በተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ እና የመንግስት ግብር ከፍለው ያጠናቀቁ መሆን አለባቸው፡፡
|
ተ.ቁ |
መግለጫ |
መለኪያ |
ብዛት |
ምርመራ |
|
1. |
የሴት ኮትና ሱሪ ሙሉ ልብስ ስፌት በሙሉ ገበር |
ሙሉ ልብስ |
326 |
የገበር ጨርቅ ከተጫራች ይሆናል |
|
2. |
የሴት ኮትና ጉርድ ቀሚስ ስፌት በሙሉ ገበር |
--- |
||
|
3. |
የወንድ ሙሉ ልብስ ስፌት ኮትና ሱሪ በሙሉ ገበር |
444 |
3. በተጫራቾች የሚቀርበው የስፌት ዋጋ በደንብ ሊነበብ በሚችል የእጅ ጽሑፍ ወይም በኮምፒዩተር ተጽፎ መቅረብ ይኖርበታል። ስርዝ ድልዝ ያለበት ሰነድ ከጨረታው ውጭ ይሆናል፡፡
4. ተጫራቾች የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ከሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በሥራ ሰዓት (ከጠዋቱ 2፡00 እስከ 6፡00 ሰዓት እና ከሰዓት 7፡00 እስከ 11፡00 ሰዓት) በአዋሽ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 01540000544500 በማንኛውም የባንኩ ቅርንጫፍ ብር 500.00 (አምስት መቶ) ገቢ በማድረግ በአዋሽ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት ሕንፃ 12ኛ ፎቅ በሚገኘው የባንኩ ግዥ ዋና ክፍል ቢሮ በአካል ቀርበው መውሰድ ይችላሉ፡፡
5. በተጫራቾች የሚቀርበው ዋጋ የእጅ እና የገበር ዋጋን ያካተተ መሆን አለበት፡፡
6. ተጫራቾች የሚያስገቧቸውን ኦሪጂናልና ኮፒ የቴክኒካል እና የዋጋ ሰነዶች ለየብቻ (ለየቅል) በታሸገ ኤንቨሎፕ በእለቱ በሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. እስከ ከሰዓት በኋላ 8፡00 ሰዓት ድረስ በአዋሽ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት ሕንፃ 12ኛ ፎቅ በሚገኘው የባንኩ ግዥ ዋና ክፍል ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
7. ጨረታው በሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ 8፡30 ሰዓት በተራ ቁጥር 4 ላይ በተጠቀሰው አድራሻ ይከፈታል።
8. ከላይ ከተራ ቁጥር 1–6 የተገለጹትን መስፈርቶች ያላሟሉ ተጫራቾች ከጨረታው ውጭ ይሆናሉ።
9. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0115-57-11-07 ወይም 0115-57-00-84 በመደወል መጠየቅ ይችላሉ።
10. ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
