አዋሽ ባንክ አ.ማ በፅህፈት ሥራ ሳይ ሳልተሰማሩ የባንኩ ሰራተኞች የደንብ ልብስ ማሰፋት ይፈልጋል፡፡
አዋሽ ባንክ አ.ማ
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር RE-AB/002/2026-27.
1. አዋሽ ባንክ አ.ማ በፅህፈት ሥራ ሳይ ሳልተሰማሩ የባንኩ ሰራተኞች የደንብ ልብስ ማሰፋት ይፈልጋል፡፡
2. በዚሁ መሠረት በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ በመስኩ የታደሰ ንገድ ፍቃድ ያሳቸው በተጨማሪ እሴት ታክስ መመዝገባቸውን የሚገልፅ ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ እና የመንግስት ግብር ከፍለው ያጠናቀቁ መሆን አለባቸው::
|
ተ/ቁ |
መግለጫ |
መለኪያ |
ብዛት |
ምርመራ |
|
1 |
የሴት ኮት እና ሱሪ ሙሉ ልብስ ስፌት በሙሉ ገበር |
ሙሉ ልብስ |
326 |
የገበር ጨርቅ ከተጫራች ይሆናል |
|
2 |
የሴት ኮት እና ጉርድ ቀሚስ ስፌት በሙሉ ገበር |
|||
|
3 |
የወንድ ሙሉ ልብስ ስፌት ኮት እና ሱሪ በሙሉ ገበር |
444 |
3. በተጫራቾች የሚቀርበዉ የስፌት ዋጋ በደንብ ሊነበብ በሚችል የእጅ ፅሁፍ ወይም በኮምፒዩተር ተፅፎ መቅረብ ይኖርበታል:: ስርዝ ድልዝ ካለዉ ከጨረታ ዉጪ ይሆናል::
4. ተጫራቾች የተዘጋጀዉን ሰነድ ከሐምሌ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በስራ ሰዓት ከጠዋቱ 2:00 እስከ 6:00 ሠዓት ከሰዓት ከ 7:00 አስከ 11:00 ሰዓት ድረስ በአዋሽ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 01540000544500 በየትኛዉም የባንኩ ቅርንጫፍ ብር 500.00 (አምስት መቶ) ገቢ በማድረግ ለዋሽ ባንክ ዋና መ/ቤት ህንፃ 12ኛ ፎቅ በሚገኘው የባንኩ ግዥ ዋና ክፍል ቢሮ በአካል ቀርቦ መዉሰድ ይችላሉ፡፡
5. በተጫራቾች የሚቀርበዉ ዋጋ የእጅ እና የገበር ዋጋን ያካተተ መሆን አለበት::
6. ተጫራቾች የሚያስገቧቸውን ኦርጂናል እና ኮፒ የቴክኒካል እና የዋጋ ሠነዶች ለየብቻ (ለየቅል) በታሸገ ጴንቨሎፕ በዕለቱ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከሠዓት በኋላ እስከ 8:00 ሰዓት ድረስ አዋሽ ባንክ ዋና መ/ቤት ህንፃ 12ኛ ፎቅ በሚገኘው የባንኩ ግዥ ዋና ክፍል ቢሮ ስዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው::
7. ጨረታው በእለቱ ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ከሠዓት በኋላ 8:30 ሰዓት ከላይ በተራ ቁጥር 4 ላይ በተጠቀሰው አድራሻ ይከፈታል::
8. ከላይ ከተራ ቁጥር 1-6 ያሉትን መስፈርት ያላሟሉ ተጫራቾች ከጨረታ ዉጪ ይሆናሉ::
9. ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0115-57-11-07 ወይም 0115-57-00-84 ደውለዉ መጠየቅ ይችላሉ::
10. ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
