የኮተቤ ብርሃነ ህይወት አጸደ ህጻናት እና የመ/ደ/ት/ቤት ለ2019 ዓ.ም የደንብ ልብሶች ፣የተለያዩ አላቂ ቢሮ ዕቃዎች እና አላቂ የትምህርት ዕቃዎች እና የፅዳት ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂይ
መስያ ቁጥር ኮ/ብ/ህ/ቅ/አ/አ/እና መካ/ደ/ት/ቤት 01/2018
የኮተቤ ብርሃነ ህይወት አጸደ ህጻናት እና የመ/ደ/ት/ቤት ለ2019 ዓ.ም የደንብ ልብሶች ፣የተለያዩ አላቂ ቢሮ ዕቃዎች እና አላቂ የትምህርት ዕቃዎች እና የፅዳት ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
1. የደንብ ልብስ ሎት 1 ለጨረታ የሚያሲዙት የብር መጠን 20,000
2. አላቂ የቢሮ ዕቃ ሎት 2 ለጨረታ የሚያሲዙት የብር መጠን 20,000
3. አላቂ የህከምና ዕቃ ሎት 3 ለጨረታ የሚያሲዙት የብር መጠን 4,000
4. ለህትመት ሎት 4 ለጨረታ የሚያሲዙት የብር መጠን 20,000
5. አላቂ የትምህርት ዕቃ ሎት 5 ለጨረታ የሚያሲዙት የብር መጠን 19,000
6. የፅዳት ዕቃዎች ሎት 6 ለጨረታ የሚያሲዙት የብር መጠን 16,000
7. የተለያዩ መሳሪያዎች ሎት 7 ለጨረታ የሚያሲዙት የብር መጠን 30,000
8. ለፕላንት ማሸነሪ መግዣ ሎት 8 ለጨረታ የሚያሲዙት የብር መጠን 30,000
9. ለህንፃ ቁሳቁስ እና ተገጣጣሚዎች መግዣ ሎት 9 ለጨረታ የሚያሲዙት የብር መጠን 26,000
* ሲሆን ተጫራቾች በመንግስት ግዥ እና ንብረት ኤጀንሲ ድረ ገጽ በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ፡፡
* በሚወዳደሩበት ዘርፍ የታደሰ የንግድ ፍቃድ እና የቫት ተመዝጋቢ እንዲሁም ህጋዊ ደረሰኝ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
* የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 400 ብር በየሎቱ በመክፈል ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 (አስር) የስራ ቀናት ውስጥ ከመስርያ ቤቱ ረዳት ፋይናንስ ቢሮ መውሰድ ይችላሉ።
* ተጫራቾች ሰነድ ለማስገባት ሲመጡ ዋናውንና ፎቶ ኮፒ ለየብቻ በታሸገ ኢንቨሎፕ የድርጅቱን ማህተም በማድረግ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
* የጨረታ ማስከበርያ ከታወቁ ባንኮች የሚሰጥ ሲፒኦ ብር (CPO) ከላይከተዘረዘሩት ሎቶች መሰረት ለእያንዳንዱ በተቀመጠው ብር መጠን መሰረት ወይም በጥሬ ገንዘብ ከሚቀርበው አጠቃላይ ዋጋ ጋር ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለበት ለጥቃቅን እና አነስተኛ ተቋማት ከአቋቋማቸው አካል ህጋዊ የዋስትና ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው፡፡
* የጨረታ ማስታወቂያው አየር ላይ በዋለ በአሥረኛው ቀን 11፡30 (አስራ አንድ ሰዓት ተኩል) ተዘግቶ በአስራ አንደኛው ቀን 3፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በት/ቤቱ ግዥ ቢሮ ይከፈታል፡፡
* ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት ንብረት ሳንፕል ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ማቅረብ አለባቸው፡
* አሸናፊ ተጫራቾች ማሸነፋቸውን በተገለፀበት በ7ቀን ውስጥ ውል መፈፀምና ላለፉበት ዕቃ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ (CPO) ማስያዝ የሚችል መሆን አለበት፡፡
* ት/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው፡፡
ስተጨማሪ መረጃ፡- አድራሻ ኮተቤ ቅዱስ ገብርኤል ቤተከርስቲያን
በስተቀኝ 400 ሜትር ገባ ብሎ
ስልክ 0118664742/011866473/0977083207
የኮተቤ ብርሃነ ህይወት አጸደ ህጻናት እና የመ/ደ/ት/ቤት
