የኮልፌ ቀራንዮ ከ/ከተማ አስተዳደር ከዚህ በታች የተጠቀሰው የአገልግሎት ግዥ ለ2019 በጀት ዓመት አወዳድሮ አገልግሎት ለመፈጸም ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር 01/2019
የኮልፌ ቀራንዮ ከ/ከተማ አስተዳደር ከዚህ በታች የተጠቀሰው የአገልግሎት ግዥ ለ2019 በጀት ዓመት አወዳድሮ አገልግሎት ለመፈጸም ይፈልጋል፡፡
ሎት 1 የመኪና ኪራይ
ሎት 2 የህትመት ሥራ አገልግሎት
ሎት 3 ዲኮር መድረክ እና ድንኳን ኪራይ
ሎት4. የኤሌክትሮኒከስ ጥገና
ሎት 5.የኬተሪንግ አገልግሎት
ሎት6. የመኪና ጥገና
ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ድርጅቶችና ግለሰቦች በጨረታው እንዲሳተፉ ይጋበዛሉ፡፡ በዚህም መሰረት ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ሁኔታዎች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡
7. አግባብነት ያለው የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ የቫት ተመዝጋቢዎች የሆኑ።
8. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ1ዐ ተከታታይ የስራ ቀናት በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ ፑል አስተዳደርና ፋይናንስ ጽ/ቤት ግዥ ቡድን በመገኘት የማይመለስ ብር400.00 (አራት መቶ ብር ብቻ) በመከፈል የጨረታዉን ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
9. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሚጫረቱበት የጨረታ ሎት ዓይነት ህትመት 20,000 (ሀያ ሺህ ብር) መኪና ኪራይ 50,000 (ሀምሳ ሺህ ብር) ዲኮር መድረክ እና ድንኳን ኪራይ 30.000 (ሰላሳ ሺህ ብር) ኤሌክትሮኒከስ ጥገና 10,000 (አስር ሺህ ብር) የኬተሪንግ አገልግሎት 50,000 (ሀምሳ ሺህ ብር) የመኪና ጥገና 50,000 (ሀምሳ ሺህ ብር) በባንክ በተረጋገጠ (CPO) ከዋጋ ማቅረቢያ ጋር በታሸገ ኤንቨሎፕ በተዘጋጀው ሣጥን ማስገባት አለባቸው::
10.ተጫራቾች የሚያቀርቡትን ሰነድ የስራውን ዝርዝር የሚገልጽ ቴከኒካል እና ፋይናንሻል ሰነድ ለየብቻ ዋናውን (ኦርጅናል) እና የማይከፈት ኮፒ በታሸገ ፖስታ የድርጅቱን ስምና አድራሻ በመጥቀስ የድርጅቱ ማህተም ያረፈበትን ፖስታ ከላይ በተጠቀሰው ቢሮ ለዚህ አገልግሎት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዛው ቀን 4፡30 ላይ ይከፈታል የጨረታው መከፈቻ ቀን በዓል ከሆነ በማግስቱ ባለው የስራ ቀን 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ 4፡30 ይከፈታል፡፡
11. ተጫራቾች የሚያቀርቡበት የነጠላ ዋጋ በሰነዱ ላይ በመግለጽ ሙሉ አድራሻና ማህተም መጠቀም አለባቸው::
12.የተሻለ አማራጭ ዘዴ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ማሳሰቢያ፡ 1ሙሉ ኦርጅናል የጨረታ ሰነድ ዋጋ ተሞልቶበት ህጋዊ ማህተም እና በየገፁ ፊርማ ተደርጐበት መመለስ አለበት ካልተመለሰ ከጨረታ የሚሰረዝ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
2.ለህትመት ስራ ሳምፕል መቅረብ አለበት
አድራሻ፦ ቤተል ከጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አጠገብ ያለው ህንጻ ላይ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ አስተዳደርዋና ስራ አስፈጻሚ ፑል የአስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት ግዥ ቡድን 8ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 02
ስልክ ቁጥር 0118-34-09-79
የኮልፌ ቀራንዮ ክ/ከተማ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ፑስ የአስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት
