የማሽነሪ ጎማ እና መለዋወጫ ግዥ
የማሽነሪ ጎማ እና መለዋወጫ ግዥ የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በከሚሴ ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት በጽ/ቤቱ ሥር ለሚገኙት ለሁሉም ማሽነሪዎች የሚውል የጎማ እና መለዋወጫ እቃዎች ግዥ ለመፈፀም በዘርፉ የንግድ ፈቃድ ያላቸውን ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ሎት 1 የማሽነሪ መለዋወጫ ዕቃዎች ግዥ
ሎት 2 የማሽነሪ ጎማ ግዥ
ስለሆነም በጨረታው ለመሳተፍ ፈቃደኛ የሆኑ፡-
- ለሥራው ሕጋዊ ፈቃድ ኖሯቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉና ያሳደሱ፤ ለሥራው የምዝገባ የምስክር ወረቀት ያላቸው፤ የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸው ግዥው ከ200,000 ሺህ ብር በላይ የሆነ የቫት ተመዝጋቢ የሆነ መሆን አለበት።
- የጨረታው ሰነድ ከከሚሴ ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 33 በግዢ/ፋይ/ንብ/አስ/ዋና የሥራ ሂደት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለ15 /ለአስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት ከላይ የተዘረዘሩትን መረጃዎች ዋናና ኮፒ በመያዝ ዘወትር በሥራ ቀንና ሰዓት ለእያንዳንዱ ሰነድ የማይመለስ የኢትዮጵያ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ በመከፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋና እና ኮፒ በማድረግ በታሸገ ኤንቨሎፕ በከሚሴ ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት በግዢ/ፋይ/ንብ/አስ/ዋና የሥራ ሂደት ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በአስራ ስድስተኛው /16/ ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት እስከ 4፡00 ሰዓት ድረስ የጎማ እና መለዋወጫ እቃዎች ግዥ ጨረታ ሰነድ ባለው ጊዜ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው 22/12/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 የማሽነሪ ጎማ እና መለዋወጫ እቃዎች ግዥ ላይ በግዢ/ፋይ/ንብ/አስ/ዋና የሥራ ሂደት ቢሮ ተጫራቾች ወይንም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- ተጫራቾች ተመላሽ የሚደረግ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ገንዘብ
ሎት 1 – 30,000 /ሰላሳ ሺህ ብር/
ሎት 2፡- 30,000 /ሰላሳ ሺህ ብር/ በጥሬ ገንዘብ ወይንም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ /CPO/ ማስያዝ አለባቸው። - ለማሽነሪ ጎማ እና መለዋወጫ እቃዎች ግዥ የጨረታ አሸናፊ የሆነው ድርጅት ውል በሚዋዋልበት ጊዜ የውለታ ማስከበሪያ ከአጠቃላይ ድምር ዋጋ 10% ማስያዝ ይኖርበታል።
- መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ፤ በከሚሴ ከተማ እና መሰረተ ልማት ጽ/ቤት በግንባር በመቅረብ ወይንም በስልክ ቁጥር 033 554 0255 ደውለው መረዳት ይችላሉ።
በከሚሴ ከተማ አስተዳደር ከተማ እና መሠረተ ልማት ጽ/ቤት
✨ messages.ai_summary
Open tender for procurement of machinery tires and spare parts, divided into two lots: Lot 1 (spare parts) and Lot 2 (tires). Bidders must hold a valid trade license, current tax clearance, registration certificate, VAT registration, and TIN.
