በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን በዳዎ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለወረዳው መንግስታዊ መስሪያ ቤቶች በ2019 በጀት ዓመት የጽሕፈት መሣሪያዎች የደንብ ልብሶች፣ የተለያዩ አልባሣት፣ የጽዳት መሳሪያች፣ የቢሮ የጽህፈት መሳሪያ ዕቃዎች(ፈርኒቸሮች)፣ልዩ ልዩ _ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ የትምህርት ሙያ ስልጠና መሳሪያዎች እንዲሁም የመኪና ሞተር ቢስከሌቶች ጎማ ግዢ ከአገርውስጥ ተጫራቾች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት
የግዥ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር -01/2019
የጨረታ ቁጥር፡-ጫ-01/2019
በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን በዳዎ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለወረዳው መንግስታዊ መስሪያ ቤቶች በ2019 በጀት ዓመት የጽሕፈት መሣሪያዎች የደንብ ልብሶች፣ የተለያዩ አልባሣት፣ የጽዳት መሳሪያች፣ የቢሮ የጽህፈት መሳሪያ ዕቃዎች(ፈርኒቸሮች)፣ልዩ ልዩ _ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች፣ የትምህርት ሙያ ስልጠና መሳሪያዎች እንዲሁም የመኪና ሞተር ቢስከሌቶች ጎማ ግዢ ከአገርውስጥ ተጫራቾች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ስለሚፈልግ በጨረታው መሰረት ለመሳተፍ የሚፈልግ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መማሪያዎች አሞልቶው መገኘት ይኖርባቸዋል፡፡
1. በንግዱ ዘርፍ የዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ሥራ ፍቃድ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፡፡
2. የመንግስት ግብር መከፈላቸውን የሚያረጋግጥ ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት ወቅታዊ የሆነ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፡፡
3. በመንግስት ዕቃ አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተካተቱና የቲን እና የቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፡፡
4. ለጨረታው ማስከበሪያ ዋስትና ለሎት አንድ ደንብ ልብስ 8000.00 ብር (ስምንት ሺ ብር) ለሎት ሁለት የጽህፈት መሳሪያዎች 10,000.00 ብር(አሥር ሺ ብር) ለሎት ሶስት የጽዳት ዕቃዎች 3000.00 ብር(ሦስት ሺ ብር) ለሎት አራት የመኪና ጎማዎች 12,000.00 ብር(አሥራ ሁለት ሺ ብር) ለሎት አምስት ፈርኒቸሮች ና የኤሌከትሮንከስ ዕቃዎች 15,000.00 ብር (አሥራ አምስት ሺ ብር)ለሎት ስድስት የትምህርት ናሙና ስልጠና መሳሪያዎች 3000.00ብር (ሦስት ሺ ብር) ህጋዊ ከሆነ ባንክ የተረጋገጠ CPO ከሚያቀርባቸው ሰነዶች ጋር መያያዝ አለባቸው፡፡
5. ተጫራቾች የዕቃዎቹን ዝርዝር በየዕቃው ምድብ ዓይነት (ሎት) ለደንብ ልብሶች፣ ለጽህፈት መሳሪያዎች፣ ለፈርኒቸሮች፣ ለኤሌክትሮንከስ ዕቃዎች ለእያንዳንዳቸው ሎት የማይመለስ ብር 400(አራት መቶ ብር) እና ለሌሎች ሎት 200.00(ሁለት መቶ ብር) በመከፈል ማስታወቂያው
6. ተጫራቾች የሚያቀርቡትን ዋጋ ሰነድ ኦርጅናልና ኮፒውን እስፔስፍኬሽን (Specification) ሳይቀየር ለየብቻው በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ከላይ በተራ ቁጥር 5 በተጠቀሰው አድራሻ ለዚሁ ጉዳይ በተዘጋጀው ሳጥን እስከ ነሐሴ 21/2018 ዓ.ም በሥራ ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
7. ጨረታው ነሐሴ 22/2018 ዓ.ም ከቀኑ 5፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዛውኑ ዕለት 5፡30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ወይም ሁለቱንም ካልተገኙ ታዛቢዎች በሚገኙበት ጨረታው ከላይ በተጠቀሰው ቁጥር 5 በተገለጸው ቦታ ይከፈታል፡፡
8. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዕቃዎች ናሙና ለማቅረብ ከሚያስቸግሩ እቃዎች ውጭጨረታው ከመከፈቱ በፊት ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
9. አሸናፊው ባአሸነፈባቸው ዕቃዎች ላይ 10/አሥር/ በመቶ ፐርሰንት የውል ማስከበሪያ በህጋዊ ባንክ የተረጋገጠ CPO በማስያዝ ማሸነፉ ከተገለጸለት ቀን ጀምሮ በ10 አሥር ቀናት ውስጥ ዳዎ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በማግኘት ውል መፈረም ይኖርባቸዋል፡፡
10. ከላይ በተራ ቁጥር 8 ላይ በተቀመጠው ጊዜ ውስጥ ውል የማይፈፀም አሸናፊ የጨረታው ማስከበሪያ ያስያዘወ ገንዘብ ለመንግሥት ገቢ የሚደረግ ሆኖ ድርጅቱ የተሻለ አማራጭመጠቀም ይችላል፡፡
11. አሸናፊው ውል ፈርሞ በውል ስምምነት መሠረት ከላይ በተገለጸው አድራሻ በራሱ ትራንስፖርት እቃዎቹን አቅርቦ ማስረከብ ይኖርበታል፡፡
12. በጨረታው ውል መሠረት እቃዎቹ በሙሉ ካስረከበ ከፍያው ወዲያው ይፈፀማል፡፡
13. መሥሪያ ቤቱ የሚያጫረታቸውን ዕቃዎች ብዛት እንደአስፈላጊነታቸው በመጨመር ወይም በመቀነስ ወይም ከውስጡበት መተው ማዘዝ ይችላል፡፡
14. ተጫራቾች በሰነዶቻቸው ላይ ስማቸውን ሙሉ አድራሻቸውን የስልክና ሞባይል ቁጥርበትከከል ጽፍው ማህተም በማድግ መፈረም አለባቸው፡፡
15. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የጠበቀ ነው፡፡
ስተጨማሪ ማብራሪያ ስልክ ቁጥር 0921148358/0979056418
የዳዎ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
