በኦሮሚያ ከልላዊ መንግስት የምስ/ሐ/ዞን የባቢሌ ወረዳ ገ/ጽ/ቤት በ 2018 የበጀት ዓመት በወረዳው ውስጥ ለሚገኙ ባለበጀት የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚሆን የተለያዩ የፅህፈት መሣሪያ ፤ የደንብ ልብስ የተለያዩ ቋሚ እቃ እና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች (የሞተር ሳይክል እና መኪና መለዋወጫ ዕቃዎች አገልግሎት የሚውሉ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በኦሮሚያ ከልላዊ መንግስት የምስ/ሐ/ዞን የባቢሌ ወረዳ ገ/ጽ/ቤት በ 2018 የበጀት ዓመት በወረዳው ውስጥ ለሚገኙ ባለበጀት የመንግስት መስሪያ ቤቶች የሚሆን የተለያዩ የፅህፈት መሣሪያ ፤ የደንብ ልብስ የተለያዩ ቋሚ እቃ እና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች (የሞተር ሳይክል እና መኪና መለዋወጫ ዕቃዎች አገልግሎት የሚውሉ እቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታው መስፈርት
- ተጫራቾች የአቅራቢነት ምዝገባ ወረቀት ያላቸውና የዘመኑን ግብር ያጠናቀቁ ወይም ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ክሊራንስ እንዲሁም የተጨማሪ ዕሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚገልጽ የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የፅህፈት መሣሪያ ፣የደንብ ልብስ የተለያዩ ቋሚ እቃ እና የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች የሚገልጽ ንግድ ፈቃድ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የተለያዩ የጨረታ እቃዎችን ዝርዝር የሚገልጽ የጨረታውን ሰነድ ጨረታው ከወጣበት ቀን 14/1/2017 ጀምሮ በተከታታይ አስራ አምስት (15) ባሉት የስራ ቀናት ውስጥ ከባቢሌ ወረዳ ገ/ጽ/ቤት የማይመለስ ብር 500.00 በመክፈል የጨረታውን ሰነድ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ አጠቃላይ ሰነድ ቢድ ቦንድ ብር 10,000.00 በባንክ የተረጋገጠ CPO ብቻ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። በተጨማሪም በማይክሮ የተደራጁ ማህበራት ከሆኑ ካደራጃቸው መስሪያ ቤት የዋስትና ደብዳቤ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን የጨረታ ሰነድ ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግ በባቢሌ ወረዳ ገ/ፅ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ የጨረታውን ሰነድ 3/12/2017 እስከ ቀኑ 6፡00 ማስገባት የሚችሉ መሆኑን እና ጨረታው በ3/12/2017 ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚያው ቀን በ3/12/2017 ከቀኑ 8፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- የጨረታው አሸናፊ ያሸነፈውን ዕቃ በሚደረገው ስምምነት መሰረት በራሱ ትራንስፖርት እስከ ባቢሌ ወርዳ ገ/ጽ/ቤት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ጨረታ በሚከፈትበት ቀን በጨረታው ውስጥ የተጠቀሱትን የኮምፒውተር ቀለም፣ኮምፒውተር ወረቀት ፣ ፎቶኮፒ ቀለም ፤ ደምብ ልብስ፣ ስክሪፕቶ ፤ የወንድና የሴት ጫማ እና ባለወንፊት ማናጄሪያል ወንበር ዓይነት ለናሙና አንድ አንድ ፍሬ ማምጣት ይኖርባቸዋል።
- የጨረታው ሰነድ ስርዝ ድልዝ ያለው ከሆነ ከጨረታ ውጪ ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች የገዙት እያንዳንዱ ሰነድ ገጽ ላይ ማህተምና ፊርማ ማድረግ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ስለሚያቀርቡት እቃ የጥራት ደረጃ ጥራቱ ከሐገር ውስጥ ጥራት ደረጃ የተረጋገጠ መሆን አለባቸው።
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ማሳሰቢያ፡- መስሪያ ቤቱ አሸናፊውን ለመለየት በጥቅል ወይም በእያንዳንዱ ዋጋ ላይ ተመስርቶ ሊያወዳድር ይችላል።
ለተጨማሪ መረጃ በስልከ ቁጥር 0938-56 26 98/ 0913-51 29 52/0912390968
በምስ/ሐ/ዞን የባቢሌ ወረዳ ገ/ጽ/ቤት
