የጅማ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት በዞን ደረጃ ለሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት ላይ የሚውሉትን የተለያዩ ቋሚና አላቂ ዕቃዎችን፤ የጽሕፈት መሣሪያዎች፤ የፅዳት ዕቃዎች፤ የኤሌክትሮኒክስ፤ ጎማ እና ባትሪ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የግዢ ጨረታ ማስታወቂያ
የጅማ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት በዞን ደረጃ ለሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት ላይ የሚውሉትን የተለያዩ ቋሚና አላቂ ዕቃዎችን፤ የጽሕፈት መሣሪያዎች፤ የፅዳት ዕቃዎች፤ የኤሌክትሮኒክስ፤ ጎማ እና ባትሪ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ ከዚህ በታች የቀረቡትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው መሣተፍ የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን በዚህ መሠረት ተወዳዳሪዎች ማሟላት የሚገባቸው መመዘኛዎች፡-
- ለሥራ ዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ የንግድ ምዝገባ ምስከር ወረቀት ያላቸው፤
- የግብር ከፋይ ምዝገባ ማለትም Tin No ሰርተፊኬት ማቅረብ አለባቸው።
- በአቅራቢነት ለመሣተፍ የተመዘገበ የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ አለባቸው።
- የዘመኑን ግብር የከፈሉ (የ2017 ዓ.ም) ታክስ ክሊራንስ ማቅረብ የሚችል፡፡
- ተወዳዳሪዎች የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ለመሰብሰብ የተመዘገቡና የVAT ሰርተፍኬት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የሥራ ቀናት የጨረታውን ሠነድ ለእያንዳንዱ ጨረታ ሠነድ የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ) በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት ከጽ/ቤቱ ግዥ ቡድን ቢሮ ቁጥር 8 መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለፅህፈት መሣሪያዎች የኢትዮጵያ ብር 10,000.00 (አስር ሺህ) ብር፣ ለኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች የኢትዮጵያ ብር 15,000.00 (አስራ አምስት ሺህ) እና ለፅዳት ዕቃዎች ደግሞ ብር 7000.00 (ሰባት ሺህ ብር) ጎማ እና ባትሪ ብር 15,000.00 (አስራ አምስት ሺህ) በባንክ በተመሠከረለት ሲፒኦ (CPO) ማስያዝ አለባቸው።
- ተጫራቾች የሚያስገቡት መወዳደሪያ ዋጋ ታክስን አጠቃሎ የተሠራና በአፋን ኦሮሞ በተዘጋጀው የጨረታ ሠነድ ላይ ተዘጋጅቶ በቀረበው ፎርማት ላይ በታይፕ ወይም በቀለም ሞልተው መመለስ አለባቸው።
- የጨረታውን ሠነድ ሞልተው በታሸገ ፖስታ አድርገው በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ማስገባት አለባቸው፡፡
- የቴክኒካል ዶክሜንት ኦርጂናል ከሲፒኦ (CPO) ጋር ታሽጎ ከቴክኒካል ኮፒ ዶክሜነት ጋር የጨረታ ዓይነት ተገልጾ በሁለቱም ፖስታ ላይ የድርጅቱ ስምና አድራሻ ተፅፎ በአንድ ፖስታ ይገባል፡፡
- የፋይናንሻል ዶክሜንት ኦርጂናል በፖስታ ታሽጎ በፋይናንሻል ኮፒ ዶክሜንት ጋር የጨረታ ዓይነት ተገልጾ በሁለቱም ፖስታ ላይ የድርጅቱ ስምና አድራሻ ተፅፎ በአንድ ፖስታ ይገባል፡፡
- የጨረታ ሣጥኖች መዝጊያና መክፈቻ ሰዓታትን እና ቀናትን አስመልክቶ ሠነዶቹን መሸጫ ቀን ካበቃ ዕለት በኋላ በሚቀጥለው የመጀመሪያ የሥራ ቀን ከጠዋቱ ልክ በ4፡00 ሰዓት የአራቱም የጨረታ ሣጥን ይዘጋል፡፡ የፅህፈት መሣሪያዎች የጨረታ ሣጥን ተዘግቶ በዚያኑ ቀን ልክ በ4፡30 ይከፈታል፡፡ ከዚህ በሚቀጥሉት የሥራ ቀናት በተመሣሣይ ሰዓታት እና በተመሣሣይ ሁኔታ የፅዳትና ዕቃዎች የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ጎማ እና ባትሪ ዕቃዎች በተከታታይ ቀናት ይከፈታሉ፡፡
- የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ቀን ቅዳሜ እሁድ ወይም በበዓል ቀን ላይ ከዋለ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሣሣይ ሰዓት ተዘግቶ ይከፈታል፡፡
- ጽህፈት ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 0471128820 ወይም 0471110380 ወይም 047 111 10 97 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
ጅማ ዞን ገንዘብ ጽ/ቤት
