Tender Detail

Tender Details


በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በኢሉባቦር ዞን ያዮ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት በወረዳው ለሚገኙ መሥሪያ ቤቶች ከዚህ በታች የተጠቀሱትን የተለያዩ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡


                                                                             ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

 

በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በኢሉባቦር ዞን ያዮ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት በ2018 በጀት ዓመት በወረዳው ለሚገኙ መሥሪያ ቤቶች ከዚህ በታች የተጠቀሱትን የተለያዩ ዕቃዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ 

  1. የፅህፈት መሣሪያ

  2.  የሞተር ሳይክል 

  3.  የሠራተኛ ደንብ ልብስ

  4.  የተለያዩ ጎማዎች ከእነ ከለመዳሪ 

  5. የቢሮ ቋሚ ዕቃዎች / Furniture/ 

  6.  የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች

 ከዚህ በታች የተዘረዘረውን መስፈርት የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

  1.  በስራው ዘርፍ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ እና የ2017 ግብር ከፍሎ ፍቃዱን አሳድሶ ያጠናቀቀ፡፡

  2.  የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን/ ያለው፡የቫት/ ወይም ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆነ ፡፡ 

  3. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚመለሰ 30,000 (ሰላሳ ሺህ) ብር በሲፒኦ (Cpo )ለእያንዳንዱ ዶክመንት ማስያዝ የሚችል 

  4. የጨረታውን ዝርዝር መግልጫ ሰነድ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በተከታታይ ባሉት 15 (አስራ አምስት) የሥራ ቀናት የማይመለስ 500 (አምት መቶ) ብር በመከፈል ከያዮ ወረዳ ገ/ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ ቤት መውሰድ ይችላሉ፡፡  

  5. የሚወዳደሩበት ሰነድ ስርዝ ድልዝ የሌለው እና የሚነበብ መሆን አለበት ስርዝ ድልዝ ካለው ውድቅ ይሆናል፡፡ ተወዳዳሪዎች ዋጋን የሚገልፅ ሰነድ ኦርጂናል እና ኮፒውን ለየብቻ ፍቃድ እና የተለያዩ ተፈላጊ ሰነዶችን አያይዞ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡  

  6. የጨረታ አሸናፊ የሆኑ ድርጅቶች ሆነው የተመረጡ የጨረታው ውጤት በደብዳቤ ከተገለፀላቸው ቀን ጀምሮ በአስር ቀናት ውስጥ በመቅረብ ያሸነፉበትን ዋጋ 10 % ለመልካም ሥራ አፈፃፀም ዋስትና በማስያዝ ውል መፈረም አለባቸው፡፡ 

  7. ጨረታው ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ 60 (ስልሳ )ቀናት ይሆናል፡፡ 

  8. ተጫራቾች የዕቃ ዝርዝር ጨረታ መወዳደሪያ በሚያቀርቡት ዋጋ ላይ ቫት ጨምሮ ወይም ያለቫት በማለት በመጨረሻው ገጽ ላይ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል መስሪያቤቱ የዕቃውን ብዛት 20% ሊጨምር ወይም ሊቀንስ ይችላል ፡፡ 

  9.  የሰራተኛ ደንብ ልብስ ለማቅረብ የሚወዳደሩ ተወዳዳሪዎች የእቃውን ናሙና ከጨረታው ሰነድ ጋር ማቅረብ አለባቸው፡፡ 

  10. የፈርኒቸር ዕቃዎች ላይ የምትወዳደሩ ድርጅቶች እስከ መግጠም ድረስ ይሆናል፡፡

  11. በራሱ ወጪ ወይም ትራንስፖርት እስከ ያዮ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት አቅርቦ ማስረከብ አለበት፡፡ 

  12. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነድ ዘወትር በሥራ ሰዓት ዋጋ በመሙላት ለጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን በያዮ ወረዳ ገንዘብ ት/ጽ/ቤት እስከ በ15ኛው ቀን እስከ11፡30 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ 

  13. ጨረታው ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት ቆይቶ በ16ኛ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተጠናቆ በዚያው ቀን 4፡30 ሰዓት ላይ ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታ ፡፡ 

  14. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ በ4፡30 ሰዓት ላይ ይከፈታል፡፡ጨረታው በሚከፈትበት ዕለት በዓል ከሆነ ወደ ሚቀጥለው የሥራ ቀን ተላልፎ ጨረታው ይከፈታል፡፡ 

  15. መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

      ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0913353270/0964708848 

           

     በኢሉአባቦር ዞን የያዮ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት

Save Tender