በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደረ ወረዳ 7 ሰኔ ዘጠኝ የመጀመሪያ ደ/ት/ቤት ለ2018 በጀት ዓመት የሚያስፈልጋቸውን ነገሮች ብቃት ያላቸውና በመስኩ የተሰማሩ ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የግዥ መለያ ቁጥር 01/2018
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደረ ወረዳ 7 ሰኔ ዘጠኝ የመጀመሪያ ደ/ት/ቤት ለ2018 በጀት ዓመት የሚያስፈልጋቸውን
ሎት 1. የደንብ ልብስ 36,000 ሎት 6. የስፖርት እቃዎች 10,000
ሎት 2. የፅህፈት መሳሪያዎች 28,018 ሎት 7. የት/ቤት አላቂ የመ/እርዳታ መስጫ 1,200
ሎት 3. የት/ት መርጃ እቃዎች 10,000 ሎት 8. የህትመት ስራዎች 4,000
ሎት 4. የፅዳት እቃዎች 32,000 ሎት 9. ቋሚ እቃዎች 16,000
ሎት 5. የጥገና እቃዎች 14,000
ብቃት ያላቸውና በመስኩ የተሰማሩ ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል።
በዚሁ መሰረት ፡-
- በጨረታው ለመወዳደር ፍላነት ያላቸው ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ የቲን እና የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣ በጥቃቅንና አነስተኛ የተደራጃችሁ ተጫራቾች አምራችነታችሁን የሚገልፅ ደብዳቤ ማቅረብ ይኖርባችኋል፡፡
- ተጫራቾች በየሎቱ የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ከወጣበት ዕለት አንስቶ በተከታታይ 10 የሥራ ቀናት የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ሰኔ 9 የመ/ደ/ት/ቤት የፋ/ግ/ን/ደጋፊ የሥራ ሒደት ቢሮ ቁጥር 05 በመምጣት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 /አስር/ ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ የሚያቀርቡትን ዋጋ መስሪያ ቤቱ ባዘጋጀው የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ በመሙላት ለእያንዳንዱ ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ በማስቀመጥ የግዥውን አይነት በመጥቀስ እና ማህተም በማድረግ በታሸገ ፖስታ ት/ቤቱ ባዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው በ10ኛው ቀን 11፡00 ሰዓት ታሽጎ በ11ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት በት/ቤቱ የፋ/ግ/ን/ደጋፈ የሥራ ሒደት ቢሮ ቁጥር 05 ይከፈታል፡፡ የመክፈቻ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሳጥን ከመከፈቱ በፊት በተወዳደሩባቸው ከሎት 1 እስከ ሎት 8 ናሙና ማቅረብ የሚኖርባቸው ሲሆን በተያያዘው የፍላጎት መግለጫ መሰረት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- የዘገየ ተጫራችና በጨረታ መክፈቻ ላይ ያልተነበበ ጨረታ ተቀባይነት የለውም፡፡
- አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፈባቸውን እቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ግዥ ፈፃሚው መስሪያ ቤት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- መ/ቤቱ የሚያጫርተውን እቃ ብዛት እንደ አስፈላጊነቱ ለእቃ 20% ለግንባታ 25% በመጨመር ወይም በመቀነስ በድጋሚ ማዘዝ የሚችል ሲሆን ተጫራቾች ላሸነፉት ቋሚ አላቂ እቃ የ6 /ስድስት/ ወር እና ለቋሚ እቃ የ1 ዓመት ዋስትና መስጠት ይኖርባቸዋል፡፡
ለተጨማሪ ማብራሪያ ጥያቄ አድራሻ፡- በነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 7 ከካዲስኮ ወረድ ብሎ በሚገኘው ቴሌ ኮሚኒኬሽን ወደ ቀኝ በሚያስገባው መንገድ 400 ሜትር ላይ ሲሆን
የመ/ቤቱ ስልክ ቁጥር :- 011-8-88-29-10/011-8-88-29-03
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ወረዳ 7 ሰኔ ዘጠኝ የመጀመሪያ ደ/ት/ቤት
