የለገ ጣፎ ለገ ዳዲ ክ/ከ/ወረዳ ፍርድ ቤት በ2018 የበጀት አመት የተለየዩ የደንብ ልብስ፤ የጽህፈት መሣሪያዎች፣ የጽዳት ዕቃዎች፣ ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች (ፈርኒቸር)፤ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችና የመሳሰሉት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የግዢ ጨረታ ቁጥር 001/2018 ዓ/ም መመሪያ
የለገ ጣፎ ለገ ዳዲ ክ/ከ/ወረዳ ፍርድ ቤት በ2018 የበጀት አመት የተለየዩ የደንብ ልብስ፤ የጽህፈት መሣሪያዎች፣ የጽዳት ዕቃዎች፣ ቋሚ የቢሮ ዕቃዎች (ፈርኒቸር)፤ የኤሌክትሮኒክስ እቃዎችና የመሳሰሉት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ ከዚህ በታች የተገለፁትን መመሪያ መሠረት ተጫራቾች ይህንን የጨረታ መመሪያ አክብረው እንዲካፈሉ እናሳውቃለን፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመካፈል ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፋሉ፤ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው፤ ተጨማሪ እሴት ታክስ (ቫት) እና የቲን ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ወይም በሌላም በሚመለከታቸው ፈቃድ ሰጪ አካላት አቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡና የምስክር ወረቀት ያላቸው።
- ማንኛውም ተጫራች ጨረታው ከተከፈተ በኋላ በጨረታው ሰነድ ላይ የተገለጹትን ማንኛውንም ሁኔታ መለወጥ ወይም ማሻሻል ወይም ጨረታውን ትቻለው ማለት አይችልም፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበርያ ብር 10,000.00 (አስር ሺህ ብር ብቻ) በባንክ በተመሰከረለት (CPO) ማስያዝ አለባቸው።
- አሸናፊዎች በሚገቡት ውል መሰረት ለመፈጸም ለውል ማስከበሪያ ያሸነፉትን ጠቅላለ ዋጋ 10% (አስር በመቶ) ወይም (CPO) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡30 ሰዓት ድረስ በለገ ጣፎ ለገ ዳዲ ክ/ከ/ወረዳ ፍርድ ቤት ፋይናንስ ቢሮ በመቅረብ የማይመለስ 200.00 /ሁለት መቶ ብር/ ብቻ ለለገ ጣፎ ለገ ዳዲ ክ/ከ/ወረዳ ፍርድ ቤት በመክፈል ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው በጋዜጣ ላይ ከወጣ ጀምሮ እስከ መስከረም 27 ቀን 2017 ዓ/ም ከጠዋቱ 2፡30 እስከ ከቀኑ በ6፡30 ሰዓት በመስሪያ ቤቱ ቅጥር ግቢ በመቅረብ ለዚህ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ በዚሁ ዕለት ከቀኑ 6፡30 ታሽጎ በ 8፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ለለገ ጣፎ ለገ ዳዲ ከ/ከ/ወረዳ ፍርድ ቤት ፋይናንስ ቢሮ ይከፈታል፡፡ ሆኖም ባለቤቱ ወይም ህጋዊ ወኪሉ ባልተገኙበትም ይከፈታል፡፡ ነገር ግን ህጋዊ ውክልና የሌለው ሰው ምንም ዓይነት ጥያቄ ወይም ሀሳብ ማቅረብ አይችልም፡፡
- የጨረታ ሰነዱ በሰዓቱ በጨረታ ሣጥን ውስጥ ካልገባ ተቀባይነት የለውም፡፡
- የጨረታው ሠነድ አርጅናልና ኮፒው ለየብቻ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስግባት አለበት፡፡
- የጥቃቅንና አነስተኛ ማይክሮ ኢንተርፕራይዝ ለውድድር የሚቀርቡት የዘመኑን ሂሳብ ኦዲት አስደርገው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
- የጥቃቅንና አነስተኛ ማይክሮ ኢንተርፕራይዝ የጨረታ ማስከበሪ ብር 10,000.00 (አስር ሺህ ብር ብቻ) በባንክ በተመሰከረለት (CPO) ማስያዝ አለባቸው። ሆኖም ከመ/ቤቱ ጋር ውል ይፈራረማሉ፡፡
- ፍርድ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ 0116682321/0910922604/0933723568
የለገ ጣፎ ለገ ዳዲ ክ/ከ/ወረዳ ፍርድ ቤት
