በሸገር ከተማ አስተዳደር ገላን ጉዳ ክ/ከተማ የገላን ጉዳ ወረዳ ገንዘብ /ጽ/ቤት ወረዳው ስር ለሚገኘው ሴክተር መስርያ ቤቶች አገልግሎት የሚውል በ2018 ዓ.ም በመደበኛ በጀት የተለያየ የደንብ ልብስ ፣ የጽህፈት መሳሪያዎች፣ የቢሮ አላቂ ዕቃዎች፣ የፅዳት ዕቃዎች፣ ኤሌክትሮኒክሶች እና ፈርኒቸሮችን በግልጽ ማስታወቂያ በሎት ዋጋ አወዳድሮ ከአሸናፊዎች ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በሸገር ከተማ አስተዳደር ገላን ጉዳ ክ/ከተማ የገላን ጉዳ ወረዳ ገንዘብ /ጽ/ቤት ወረዳው ስር ለሚገኘው ሴክተር መስርያ ቤቶች አገልግሎት የሚውል በ2018 ዓ.ም በመደበኛ በጀት የተለያየ የደንብ ልብስ፣ የጽህፈት መሳሪያዎች፣ የቢሮ አላቂ ዕቃዎች፣ የፅዳት ዕቃዎች፣ ኤሌክትሮኒክሶች እና ፈርኒቸሮችን በግልጽ ማስታወቂያ በሎት ዋጋ አወዳድሮ ከአሸናፊዎች ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚህም መሰረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን መስፈርቶቹም፡-
- በዘርፉ ህጋዊ የተደሰ የንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚትችሉ።
- ተጫራቾች የምዝገባ የምስክር ወረቀት /Tin number/ አብሮ ማያያዝ የሚችሉና
- 200,000 ብር በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው።
- ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር ሰነድ የያዘ በሸገር ከተማ አስተዳደር ገላን ጉዳ ክፍለ ከተማ የገላን ጉዳ ወረዳ ገንዘብ/ጽ/ቤት ቢሮ 02 በማቅረብ የማይመለስ 250 /ሁለት መቶ ሃምሳ ብር/ በመክፈል ይህ ማስታወቂያ አዲስ ዘመን ጋዜጣ በአየር ላይ ከዋለበት ዕለት ጀምሮ ለ15 /አስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት ገዝተው በመሙለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ / ኤንቨሎፕ በማሸግ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው ይህ መስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አየር ላይ ከዋለበት ዕለት ጀምሮ በ16ኛው ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ከጠዋቱ 4፡00 የጨረታ ሳጥኑ በዚያው ቀን 4፡30 የሚከፈት መሆኑን እየገለጽን ሆኖም የመክፈቻ ዕለት በዓላት ላይ ከሆነ የሚቀጥለው የስራ ቀናት በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።
- ተጫራቾች ለሞሉት ለጠቅላላ የጨረታ መጠን 30,000 /ሰላሳ ሺህ/ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በጥሬ ገንዘብ ወይም በባንክ በተረጋገጠ CPO ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ለሚያቀርቡት መረጃ አርጅናልና ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ለበለጠ መረጃ የተጫራቾችን መመሪያ ላይ መረዳት ይቻላል ወይም በስልክ ቁ. 09 16 11 35 32 መደወልና መጠየቅ ይችላሉ፡፡
- አሸናፊዎች ያሸነፉበትን ዕቃ ገላን ጉዳ ወረዳ ገንዘብ /ጽ/ቤት ድረስ ማቅረብ አለባቸው። በጨረታ አሸናፊ የሆኑት ተጫራቾች ውስጥ ካስገቡ ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ በሙሉ ለመንግስት ገቢ ይሆናል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
በሸገር ከተማ አስተዳደር ገላን ጉዳ ክ/ከተማ የገላን ጉዳ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
