በሸገር ከተማ ሱሉልታ ክ/ከተማ የወሰርቢ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለሚገኙ ሴክተሮች አላቂ የጽዳት፣ ኤሌክሮኒክስ፤ ፈርኒቸር እና የደንብ ልብስ በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በሸገር ከተማ ሱሉልታ ክ/ከተማ የወሰርቢ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለሚገኙ ሴክተሮች አላቂ የጽዳት፣ ኤሌክሮኒክስ፤ ፈርኒቸር እና የደንብ ልብስ ደንብ መመሪያ /Bidders instruction/
ሀ. የተወዳዳሪዎች መመሪያ
1. ተጫራቾች በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው ሆኖ
ሀ. የዘመኑን ግብር በመክፈል የ2017/18 የታደሰ ንግድ ፈቃድ ማስረጃ
ለ. የ/ኢ/ልማት ሚኒስቴር የዕቃ አቅራቢነት የምዝገባ ማስረጃ
ሐ. የቫት ተመዝጋቢ የሆኑ መወዳደር ይችላሉ።
- ተጫራቾች ከማንኛውም የሙስናና የብክነት ድርጊቶች ነጻ የሆኑና በፌዴራልና በክልል የወጡትን የግዢ ደንቦች በማክበር ሰነዱ ውስጥ የቀረቡትን ግዴታዎች አምነውበት መፈፀም ይኖርባቸዋል፡፡
- ማንኛም ተጫራች ጨረታውን በህገወጥ መንገድ ሊያራምድ የሞከረ ከጨረታው ወጪ ከመሆኑም በላይ ለወደፊቱ በሚካሄዱ ጨረታዎች ላይ እንዳይሳተፍ ተደርጎ ያስያዘው የጨረታ ማስከበሪያ ይወረስበታል ።
- ተጫራቾች ወደጨረታው ለመቅረብ ግዴታዎቻቸውን የተወጡና የተጠየቀውን ስፔስፊኬሽን በማሟላት የወቅቱን ገበያ ያገናዘበ ዋጋ ያቀረቡ መሆን አለባቸው።
- ተጫራቾች መ/ቤቱ ባቀረበው ዕቃ ዝርዝር በሙሉ ወይም በሚፈልገውም የዕቃ ዝርዝር ላይ መጫረት ይችላሉ እንጂ ተጫራቹ የተወሰነ ዕቃ ለይቶ ማቅረብ አይችልም።
- የተወዳዳሪዎች ሀሳብ ሰነድ ሲቀርብ የዕቃው ስፔስፊኬሽን፣ የዕቃው አይነት፣ የተመረተበት ሀገር ስም፣ የዕቃው መለያ ሞዴል ቁጥር፣ የተመረተበት ዓመተምህረት ስፔስፊኬሽን ላይ መገለፅ አለበት፡፡
- አሸናፊ ተጫራቾች የቅድመ ክፍያ ከጨረታው ዕቃ 50% ገቢ ካደረጉ በኋላ ከጠቅላላው ዋጋ 30% ብቻ መጠየቅ ይችላሉ፡፡
- አንድ ተጫራች በሰጠው ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ መስጠት አይቻልም፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የሚወዳደርበትን የዕቃ አይነት የነጠላ ዋጋ ማቅረብ ይኖርበታል።
- የሚቀርበው ዋጋ የወቅቱን አካባቢ ገበያ ያገናዘበ መሆን ይገባዋል።
- የዕቃው ሞዴል ወይም ስዕል ናሙና ከጨረታ ሰነዱ ጋር ይቀርባል፡፡
- መስሪያ ቤቱ ባቀረበው ጨረታ ላይ 20% የመጨመር ወይም የመቀነስ መብት አለው።
- አሸናፊ ተጫራች የውድድሩ ውጤት ከተነገረበት 5-10 ቀን ቀርቦ ውል ካልፈጸመ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዘው ገንዘብ ይወረሳል፡፡
- የጨረታው የመወዳደሪያ ሀሳብ ሰነድ ኦሪጅናልና አንድ ፎቶ ኮፒ በተለያዩ ፖስታዎች ከተፈላጊ መረጃዎች ጋር ተያይዞ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ይቀርባል።
- የሚቀርበው ሰነድ ሙሉ አድራሻ የተጻፈበት ሆኖ በሚመለከተው ባለስልጣን የተፈረመበት እና በማህተም የተረጋገጠ መሆን አለበት።
- የጨረታውን ሰነድ ከወሰርቢ ወረዳ ገንዝብ አንድ /1/ ከጳጉሜ 03/2017 እስከ 19/01/2018 ዓ.ም 1፡30 ሰዓት ድረስ መግዛት ይቻላል።
- ተጫራቾች የጨረታውን መወዳደሪያ ሀሳብ ሰነድ የያዘ ፖስታ ጨረታውን ከገዙበት ቀን ጀምሮ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያኑ ቀን ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ተጫራች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በሰዓቱ ባይገኙም የጨረታ ሳጥኑ ይከፈታል፡፡
- ሰነዱን ለመመርመርና ለመገምገም የሚጠቅም ሆኖ ከተገኘ መስሪያ ቤቱ ተጫራቾቹ ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሀሳብ ሰነድ ላይ መግለጫ መጠየቅ ይችላል፡፡
- ጨረታውን በመመርመር ሂደት ላይ የተገኘውን የሀሳብ ስህተት ማስተካከል ይቻላል፡፡ ድርጊቱ ወዲያው የመወዳደሪያ ሀሳብ ሰነድ ላቀረበ ክፍል ይገለጽለታል፡፡
- ጨረታው ከተከፈተ በኋላ የቀረበውን የውድድር ሀሳብ መቀየር፣ ማሻሻል ወይም ከጨረታው ራስን ማግለል አይቻልም፡፡
- አሸናፊ ተጫራቾች የውል ማስከበሪያ የጨረታ ውጤት ከተነገረበት 5-10 ቀን ውስጥ ከግዥው ዋጋ ላይ 10% በባንክ በተመሰከረ ቼክ ወይም /CPO/ በማቅረብ የግዢ ውል መፈረም ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታው ማስከበሪያ አሸናፊው ከታወቀ ለተሸናፊው ይመለስለታል፡፡
- ለአሸናፊ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የውል ማስከበሪያውን ገቢ አድርገው ከጨረሱ በኋላ ይመለስላቸዋል።
- አሸናፊው ተጫራች ውል ከፈጸሙ በኋላ በ10 ቀን ውስጥ ዕቃውን አጠናቀው ማቅረብ አለባቸው።
- የጨረታው ዋጋ የጨረታው ውጤት ከተነገረበት ቀን አንስቶ ዕቃውን ማስረከቢያ ቀን ድረስ ያለምንም ለውጥ መቆየት አለበት።
- ተወዳዳሪዎች ጨረታውን ካሸነፉ ዕቃዎቹን በሙሉ በራሳቸው ትራንስፖርት ማውጫና ማውረጃ ችለው የወሰርቢ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ዕቃ ግምጃ ቤት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- የሚቀርቡት ዕቃዎች የተቀደዱ፣ የተሰበሩ፤ የተበላሹና ከአገልግሎት ውጪ ከሆኑ መስሪያ ቤቱ አይቀበላቸውም።
- መ/ቤቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊልም የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። የሰነድ መሸጫ የማይመለስ 500 ብር ብቻ ነው፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000 /ሀምሳ ሺህ ብር/ በባንክ በተመሰከረለት ቼክ ብቻ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0910821521 በዚህ ስልክ ቁጥር ደውለው የሚፈልጉትን መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
በሸገር ከተማ ሱሉልታ ክ/ከተማ የወሰርቢ ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
