የካፋ ሆን ፋይናንስና መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት በዞን ማዕከል ለሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ ለመግዛት እና መሸጥ ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡- ግ/ጨ/ቁጥር 02/2018
የካፋ ሆን ፋይናንስና መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት በዞን ማዕከል ለሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ የተለያዩ ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ተጫራቾችን በመጋበዝ እንደሚከተለው በሎት በመከፋፈል እስከ በጀት ዓመቱ ማብቂያ ማለትም እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ፡-
- ሎት 1 - ለካፋ ዞን ለፖሊስ አባላት ብርድ ልብስ ለመግዛት፤
- ሎት 2 - የተለያዩ ሞዴል ላላቸው ተሽከርካሪዎች አገልግሎት የሚውል ዘይትና ቅባት ለመግዛት፤
- ሎት 3 - የተለያዩ የደንብ ልብሶች ለመግዛት፤
- ሎት 4 - በካፋ ዞን ግብርና መምሪያ አማካይኝነት አበራ አካባቢ የሰው ሠራሽ ደን ዛፍን ለመሸጥ እና
- ሎት 5 - በካፋ ዞን ባህል ቱ/ስፖርት መምሪያ አማካይኝነት ቦንጋ ስቴዲየም አካባቢ የሰው ሠራሽ ደን ዛፍን ለመሸጥ ማወዳደር ይፈልጋል።
በዚሁ መሠረት በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች፡-
- ተጫራቾች በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ፤ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፤ የቫት፣ የቲን፣ ከገቢዎች ግብር ስለመክፈላቸው የተሰጠ ማስረጃ እና የአቅራቢነት የምስክር ወረቀት ፎቶ ኮፒ አያይዘው ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች ከላይ የተጠቀሱትን መረጃዎች የጨረታ ዶክመንት ሊገዙ ሲመጡ ኦሪጅናሉን እና የማይመለስ ፎቶ ኮፒ አቅርበው እንዲመሳከር የማድረግ ግዴታ አለባቸው። በመሆኑም ተጫራቾች ለሁሉም ሎቶች ለእያንዳንዳቸው የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 500.00 /አምስት መቶ ብር/ ካፋ ዞን ገቢዎች ባለስልጣን ቅ/ጽ/ቤት ቀርበው በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት ለተከታታይ 15 ቀናት ካፋ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ግዥ ንብ/አስ/ዳይሬከቶሬት በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ CPO ጥሬ ገንዘብ እና ቼከ
- ለሎት 1 - ለካፋ ዞን ለፖሊስ አባላት የብርድ ልብስ ብር 60,000.00 /ስልሳ ሺህ ብር/፤
- ለሎት 2 - የተለያዩ ሞዴል ላላቸው ተሽከርካሪዎች አገልግሎት የሚውል ዘይትና ቅባት ብር 60,000.00 /ስልሳ ሺህ ብር/
- ለሎት 3 - የተለያዩ የደንብ ልብሶች ብር 80,000.00 /ሰማኒያ ሺህ ብር/፤
- ለሎት 4 እና ለሎት 5 - ለእያንዳንዳቸው ብር 300,000.00 /ሦስት መቶ ሺህ ብር/ በካፋ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ስም በማሰራት ከጨረታው ሰነድ ጋር በማዘጋጀት አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በየሎት በማከፋፈል እና የሎት ቁጥሩን ሠነዱ ላይ በመጻፍ በሰም /በሙጫ/ በታሸገ ኤንቨሎፕ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15 ተከታታይ ቀናት በካፋ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ግዥ ንብ/አስ/ዳይሬክቶሬት በመቅረብ ለዚሁ ጨረታ ሥራ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ።
- የጨረታው ሳጥን በ16ኛው ቀን በ3፡30 ሰዓት ታሽጎ በዚያው ዕለት በ4፡00 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በካፋ ዞን ፋይናንስና መምሪያ ይከፈታል። የጨረታ መዝጊያ እና መክፈቻው ቀን ዝግ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይሆናል። በመክፈቻው ዕለት የተጫራቾች ወይም ህጋዊ ተወካዮች ያለመገኘት የጨረታ መክፈት ሂደት እያስተጓጉልም። 15 ተከታታይ ቀናት የተባለው ቅዳሜና እሁድ ጨምሮ የሚቆጠር ነው።
- አሸናፊው ድርጅት ከሎት 4 እና ከሎት 5 በስተቀር ከላይ በሎት የተዘረዘሩትን ዕቃዎች በሙሉ በራሱ ወጪ ካፋ ዞን ፋይናንስ መምሪያ አቅርቦ የማስረከብ ግዴታ አለበት።
- አሸናፊው ድርጅት ጨረታውን ያሸነፈበትን ጠቅላላ ድምር ዋጋ ከካፋ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በሚገለፀው የባንክ ሂሳብ ቁጥር ገቢ በማድረግ ያሸነፋቸውን የደን ዛፎችን በራሱ ወጪ በማስጫን በ30 ቀን ውስጥ ሙሉ በሙሉ ማንሳት ይጠበቅባቸዋል።
- አሸናፊው ድርጅት ከሎት 2 የተለያዩ ሞዴል ላላቸው ተሽከርካሪዎች አገልግሎት የሚውል ዘይትና ቅባት በስተቀር ከላይ በሎት የተዘረዘሩትን ተወዳዳሪ ድርጅቶች የቫት ተመዝጋቢነት ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች አሰሪው መ/ቤት ያዘጋጀውን የቴክኒካል ዶክመንት መጠይቅ ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
- ተወዳዳሪዎች ጨረታ ዶክመንት ለማስገባት ሲመጡ ከሎት 4 እና ከሎት 5 በስተቀር ሎት 1 ለካፋ ዞን ለፖሊስ አባላት ብርድ ልብስ እና ሎት 3 የተለያዩ የደንብ ልብሶች ለሚወዳደሩባቸው ዕቃዎች በሙሉ ናሙና ማቅረብ የሚኖርባቸው ሲሆን ናሙና ያላቀረበ ተወዳዳሪ ድርጅት ዋጋው አይታይለትም።
- ተጫራቾች ለሽያጭ የተዘጋጁ ሁሉንም የሰው ሠራሽ ደን ዛፍ እንጂ በተናጠል የሚፈልጉትን መወዳደር ከጨረታ ውጭ ያደርጋል።
- ገዢው በጨረታ ያሸነፈውን የደን ክልል ከተረከበ በኋላ እንዲቆረጥ የተፈቀደለትን የደን ክልል ያመረተውን ምርት የማስጠበቅ ኃላፊነት የራሱ ይሆናል።
- ለተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት CPO፣ ጥሬ ገንዘብ እና ቼክ ተመላሽ የሚደረገው ያሸነፉትን ዛፎችን ሙሉ በሙሉ ማንሳታቸው ሲረጋገጥ መሆኑ ታውቆ በወቅቱ ካልተነሳ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት CPO፣ ጥሬ ገንዘብ እና ቼክ የሚወረስ ይሆናል።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 047-3-31-18-26 በመደወል መጠየቅ ይቻላል።
የካፋ ዞን ፋይናንስ መምሪያ
