ድርጅታችን ግዮን ጋዝ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር የተለያዩ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን፤ የመኪና ባትሪዎች፤ ጎማ፣ የቢሮ ጠረጴዛ ወንበር፣ ቁርጥራጭ ብረታብረቶችን፣ ጋዜጣዎች የተሽከርካሪዎች መለዋወጫ፣ አሮጌ ቆርቆሮ የቴክኖሎጂ ዕቃዎች፣ ፕሪንተር እና የፎቶ ኮፒና የፕሪንተር የቶነር ካርትሬጆች አወዳድሮ በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ድርጅታችን ግዮን ጋዝ ኃላ/የተ/የግ/ማህበር የተለያዩ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን፤ የመኪና ባትሪዎች፤ ጎማ፣ የቢሮ ጠረጴዛ ወንበር፣ ቁርጥራጭ ብረታብረቶችን፣ ጋዜጣዎች የተሽከርካሪዎች መለዋወጫ፣ አሮጌ ቆርቆሮ፣ የቴክኖሎጂ ዕቃዎች፣ ፕሪንተር እና የፎቶ ኮፒና የፕሪንተር የቶነር ካርትሬጆች አወዳድሮ በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል።
- በጨረታ ሽያጭ ለመወዳደር የሚፈልግ ማንኛውም ተጫራች የንግድ ፍቃድ ያለው የዘመኑን ግብር የከፈለ ለመሆኑ ከገቢዎች እና ከጉምሩክ ባለስልጣን የምስክር ወረቀት እንዲሁም የግብር መለያ ቁጥር የሚያቀርብ መሆን አለበት።
- ጨረታው ንብረቱ በሚገኝበት ጎተራ በሚገኘው የግዮን ጋዝ ዋናው መ/ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ ይካሔዳል።
- ጨረታው በተቀመጠለት ሠዓት ውስጥ ካልተጠናቀቀ ላልተወሰነ ጊዜ ሊራዘም ይችላል።
- በጨረታ የሚሳተፉ ተጫራቾች ጨረታው ከመጀመሩ በፊት ተመዝግበው ለሚወዳደሩበት ተሽከርካሪ እና ንብረት የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ገንዘብ በC.P.O 500 (2%) ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ለተሽናፊዎች ያስያዙት የዋስትና ገንዘብ በ3/ሶስት/ የስራ ቀናት ውስጥ የሚመለስ ሲሆን ለአሸናፊዎች ግን ከሽያጭ ጋር የሚታሰብለት ይሆናል።
- የጨረታው አሸናፊ ማሸነፉ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ በ5 /አምስት/ የሥራ ቀናት ውስጥ ያሸነፈበትን ንብረት ዋጋ ለድርጅቱ ገቢ ማድረግ አለበት። የጨረታው አሸናፊ በተሰጠው ጊዜ ገደብ ውስጥ ገቢ ካላደረገ ለጨረታ ማከበሪያ የተያዘው ገንዘብ ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ንብረቱ በድጋሚ ለሽያጭ ይቀርባል።
- አሸናፊው ግለሰብ ወይም ድርጅት ያሸነፈበትን ገንዘብ ገቢ ባደረገ በ 7 /ሰባት/ ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ዕቃውን መረከብ ያለበት ሲሆን፣ በተሰጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ በጨረታው ያሸነፈበትን ንብረት የማንሳት ግዴታ አለበት።
ተጫራቾች ለጨረታ የቀረበውን ንብረት ዝርዝር በዚህ ሰነድ የተዘጋጀ ሲሆን ንብረቶቹን በአካል ለመመልከት
- ጎተራ ግዮን ጋዝ ዋናው መ/ቤት ፤
- ገላና የድርጀቱ የጋዝ ዲፖት ማየት ይቻላል።
- ለሽያጭ የቀረቡትን ንብረቶች ለማየት እና C.P.O ማስገቢያ ቀን እና ሰዓት በሚመለከት ከታች በሠንጠረዥ በተገለጸው መሰረት ነው።
- ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ወይም ሙሉ በሙሉ የመስረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 0114162827/0913149581 በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ይቻላል።
|
ለሽያጭ የቀረቡትን ንብረቶች ለማየት እና C.P.O ማስገቢያ ቀን ከመስከረም 5 ቀን 2018 ጀምሮ ይሆናል።
|
|
የጨረታው የሚጠናቀቅበት መስከረም 15 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 8:30 ሰአት ላይ ይሆናል።
|
