የአገና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የሚያሥፈልጉን የሥልጠና ግብዓቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር አ/ፖ/ቴ/ኮ/001/2017
የአገና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ/ክ/መ/ክልል በጉራጌ ዞን ከወልቂጤ ከተማ 42 ኪ.ሜ ከቡታጅራ 38 ኪሎ ሜትር ርቀትና ከአዲስ አበባ 196 ኪሎ ሜትር ላይ በአገና ከተማ የሚገኝ ኮሌጅ ሲሆን በ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት የሚያሥፈልጉን የሥልጠና ግብዓቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም መስፈርቱን የምታሟሉ አቅራቢዎች ከዚህ በታች በተዘረዘሩት የሥልጠና ክፍሎች ለማቅረብ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡
- የኢኮቴ (ICI) ዕቃዎች ዝርዝር
- የቢሮ የጽሕፈትና ሌሎች መገልገያ ዕቃዎች
- የMasonry ሥልጠና ክፍል ቋሚ እቃዎች
- የMechanics ሥልጠና ክፍል ዕቃዎች
- የAutomotive ሥልጠና ክፍል ዕቃዎች
- የBEI ሥልጠና ክፍል ዕቃዎች
- ተዛማጅ ሥልጠና ክፍል ዕቃዎች
- የElectro technology ዕቃዎች
- የጋርመንት ሥልጠና ክፍል ዕቃዎች
- ለሞተር ሳይክሎች የሚያስፈልጉ መለዋወጫ ዕቃዎች
- የአካባቢ ምርት ዕቃዎች
- የሰብል ልማት ሥልጠና ክፍል ዕቃዎች
- የHotel ሥልጠና ክፍል ቋሚ ዕቃዎች
- የፈርኒቸር ሥልጠና ክፍል ዕቃዎች
በመሆኑም ከላይ የተጠቀሱትን የሥልጠና ዕቃዎች ለማቅረብ የሚያስፈልጉ መስፈርቶች
- በመስኩ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸው አቅራቢዎች ማስረጃቸውን ማቅረብ የሚችሉና የዘመኑን ግብር የከፈሉ እንዲሁም የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ የሆኑ
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የሥራ ቀናት የማይመለስ ብር (600) ስድስት መቶ ብር ብቻ) በኮሌጁ አካውንት ቁጥር 1000168288248 በማስገባት ስሊፕ ይዘው መምጣት ይጠበቅባቸዋል፡፡ የጨረታው ሰነድ በኮሌጁ ግዢና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ደጋፊ የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 16 ለተከታታይ የሥራ ቀናት ከቀኑ 6:00 ድረስ መግዛት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የዘመኑ የአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ መሆን ይኖርባቸዋል
- የጨረታው ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ የሥራ ቀናት በ15ኛው ቀን 6:00 ሰዓት ላይ የጨረታ ሳጥን ታሽጎ 8:30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች የእቃውን ዋጋ የእቃውን አይነት በጨረታ ሰነዱ በተጠቀሰው መሰረት ይሆናል
- ተጫራቾች የጨረታውን ሙሉ ሰነድ ሞልተው ኦርጂናል እና ፎቶ ኮፒ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግ የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦድ 1.5% በባንክ የተመሰከረለት (CPO) በንብ ባንክ፣ በብርሃን ባንክ፣ በአቢሲኒያ ባንክ፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአገና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስም በማሠራት ኦርጅናል ዶክመንት በፖስታ ውስጥ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ሌላው ተጫራች ባቀረበው ዋጋ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም ፡፡
- ኮሌጁ የተሻለ ዘዴ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- የጨረታ አሸናፊዎች ዋናውን እቃ ከማስገባታቸው በፊት ናሙና ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ጨረታውን ያሸነፈው አካል ሕጉ በሚፈቅደው መሰረት 3% (Withholding) የመክፈል ግዴታ አለባቸው።
- የጨረታው አሸናፊዎች ያሸነፉትን ዕቃ ወደ ኮሌጁ ድረስ የማቅረብ ግዴታ አለባቸው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 0113290387/ 0113290569 ፋክስ 0113290168
Email: agenacon.indus.college@gmail.com
ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የቴክ/ሙያ ትም/ሥልጠና ቢሮ የአገና ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
