አማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት የኮምበልቻ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለሥልጣን መ/ቤት በ2018 በጀት አመት ከመደበኛ በጀት የጽህፈት መሳሪያዎች እና አላቂ (የጽዳት) እቃዎችን በሎት፡- 1 /አንድ/ እና ቋሚ እቃዎችን በሎት፡- 2 /ሁለት/ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
አማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት የኮምበልቻ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለሥልጣን መ/ቤት በ2018 በጀት አመት ከመደበኛ በጀት የጽህፈት መሳሪያዎች እና አላቂ (የጽዳት) እቃዎችን በሎት፡- 1 /አንድ/ እና ቋሚ እቃዎችን በሎት፡- 2 /ሁለት/ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
በመሆኑም የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት የምትችሉ ተጫራቾች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡
- በዘመኑና በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ሥራ ፈቃድ ያለው
- በጨረታ ለመሳተፍ የሚያገለግል ከገቢዎች የተጻፈ ማስረጃ ደብዳቤ ማቅረብ የሚችል።
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN NO) ያላቸው እና የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል።
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
- ጨረታው ጸንቶ የሚቆይበት ጊዜ የጨረታ ሰነዱ ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ለ40 ቀናት ሲሆን ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (BID BOND) ብር 8,000 (ስምንት ሺህ) ብር ለጽህፈት መሳሪያዎች እና አላቂ (የጽዳት) እቃዎች ለሎት 1/አንድ/ እና 10,000 /አስር ሺህ ብር/ ለቋሚ እቃዎች /ለሎት 2/ሁለት/ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣያ (CPO) በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ለየብቻ በማሰራት ከጨረታ ሰነዱ ጋር አብሮ ማቅረብ አለበት፡፡
- ማንኛውም ተጫራች መ/ቤቱ ባዘጋጀው የጨረታ ሰነድ በሚጠይቀው የዋጋ አሞላል ብቻ መሙላት አለበት፡፡ በሚጠይቀው የዋጋ አሞላል ካልሞሉ የጨረታ ሰነዱ ውድቅ ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- የጨረታው ውድድር የሚካሄደው በሎት በጥቅል/ድምር ውጤት ስለሆነ የማይሞላ አይተም መኖር የለበትም ያልተሞላ አይተም ከተገኘ ከጨረታ ውድቅ ይሆናሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ) ብር ለእያንዳንዱ ሎት በመክፈል ከግ/ፋይ/ን/አስ/ደ/የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 508 ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው አየር ላይ የሚቆየው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከ14/02/2018 ዓ.ም እስከ 28/02/2018 ዓ.ም 11፡30 ሰዓት ድረስ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወጥ በሆነ አንድ ቅጅ ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ መንገዶች ባለሥልጣን መ/ቤት በግዥና ፋይ/ን/አስ/ደ/የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 508 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት እስከ ቀን 29/2/2018 ዓ/ም በ 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥና ፋይ/ን/አስ/ደ/የሥራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 508 በ29/02/2018 ዓ.ም በ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በ 4፡30 ላይ ይከፈታል። ነገር ግን ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ቅዳሜ ፤እሁድና የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት መሆኑን እንገልጻልን፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰርዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ለበለጠ መረጃ በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለሥልጣን መ/ቤት በአካል በመቅረብ ወይንም በስልከ ቁጥር 033 351 37/033 551 05 04/ መጠየቅ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
- ማሳሰቢያ:- ሁሉም ተጫራቾች በተጫራቾች መመሪያ መሰረት የማጭበርበር ድርጊት ላለመፈጸም ቃል የሚገቡበትን ቅጽ ፈርሞ የድርጅቱን ማህተም በመምታት ጨረታ ሰነዱ ጋር ማስገባት አለበት፡፡ የመስሪያ ቤቱ አድራሻ ኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ህንጻ አምስተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 508 ላይ ነው።
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለሥልጣን
