የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የተለያዩ አቃዎች ግዢ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የተለያዩ አቃዎች ግዢ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
- የተለያየ መጠን ያላቸው የተሸከርካሪ ጎማዎች እና በልቦች፣ የተለያየ መጠን ያላቸው ብረታ ብረቶች እና ሌሎች እቃዎች፣ የተለያዩ የቧንቧ ዕቃዎች ግዥ፣
- የሸሆና ጥፍር መንቀያ /Hooves Remover/ ግዥ፣
- ከ5-8ቶን ክብደት የሚሸከም ሻንሲ ካቢን ግዥ፤
- የጥበቃ አገልግሎት ግዥ፤
- የወንዶችና የሴቶች ልብስ ስፌት አገልግሎት ግዥ፣
ማንኛውም ተጫራች፡-
- በዘርፉ ወደም በተመሳሳይ ህጋዊና የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያለው ለተጨማሪ እሴት ታክስ ከፋይነት የተመዘገበ መሆኑን እና የታክስ ክፍያ መለያ ቁጥር (TIN) የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት፤ የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ ተጫራቾች ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ ስለመሆናቸው በግብር ሰብሳቢው ባለስልጣን የተሰጠ በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል የታደሰ ክሊራንስ እንዲሁም በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ መመዝገባቸውን የሚገልፅ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፤
- ለእያንዳንዱ የጨረታ ዓይነት የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል በስራ ሰዓት ከግዥና ንብረት አስተዳደር የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 30 ዝርዝር መረጃ የያዘውን የጨረታ ሠነድ ማግኘት ይችላል፣
- የጨረታ ማስከበሪያ /ቢደ ቦንድ/ ለሚጫረትበት የጠቅላላ ዋጋውን 2% በሲ.ፒ.ኦ፣ በባንክ ጋራንቲ ወይም በጥሬ ገንዘብ በድርጅቱ ደረሰኝ ማስያዝ ይኖርበታል፣
- የጨረታ ሰነዶችና ከጨረታው ጋር ተያያዠ የሆኑ ሠነዶችን በፖስታ በማሸግ ከጨረታ መዝጊያው ሰዓት በፊት ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለበት፣
- ጨረታው ህዳር 9 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4:30 ሰዓት የጨረታ ኮሚቴዎች፣ ሁሉም ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በድርጅቱ ውስጥ ይከፈታል።
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 011466-47-05 መጠየቅ ይቻላል።
የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት
