የአዲስ አበባ ከተማ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን ከታች በሎት የተዘረዘሩትን እቃዎች ግዢ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር፡- አአትማባ/ብግጨ/ግዳ/ዕቃ/04/2018
የአዲስ አበባ ከተማ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን ከታች በሎት የተዘረዘሩትን እቃዎች ግዢ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም፡-
የትራፊክ ቁጥጥር ሰራተኞች የደንብ ልብስ፣ የቆዳ ቦርሳ፣ ጉርድ እና ቡትስ ቆዳ ጫማ፣ ባለገበር አንጸባራቂ ሰደርያ እና ፊሽካ፡፡
ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ድርጅቶች፡-
- የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር) የማይመለስ በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ ጨረታው መዝጊያ ቀን ዘወትር በሥራ ሰዓት ጠዋት ከ2፡00 እስከ 6፡30 ከሰዓት ከ7፡30 እስከ 10፡00 ሰዓት በባለስልጣኑ ግዥ ንብረት አስተዳደር እና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 10-01 መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የቫት ተመዝጋቢ፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና ለሚያቀርቡት አገልግሎት ዘርፍ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው።
- ተጫራቾች በእቃ አቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ ስለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ለጨረታው ማስከበሪያ በባንክ በተመሰከረለት ቼክ (ሲፒኦ) ተመላሽ የሚሆን 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) ማስያዝ አለባቸው።
- የጨረታው አሸናፊ ሆነው የተመረጡት ድርጅቶች የጨረታው ውጤት በደብዳቤ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ በ10 (አስር) የሥራ ቀናት ውስጥ በባለሥልጣኑ ግዥ ንብረት አስተዳደር እና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዋና ክፍል በመቅረብ ያሸነፉበትን ዋጋ 10% የመልካም ሥራ አፈጻጸም በማስያዝ እና ውል መፈረም አለባቸው።
- የጨረታው አሸናፊ ላልሆኑ ድርጅቶች ለጨረታ ማስከበሪያ ያስያዙት ሲፒኦ የጨረታው አሸናፊ ተለይቶ የአሸናፊነት ደብዳቤ ከተሰጠው በኋላ ባሉት 5 ቀናት ውስጥ ይመለስላቸዋል፡፡
- ጨረታው ኅዳር 11/2018 ዓ.ም በ8፡00 ሰዓት ይዘጋል፡፡
- ጨረታው ኅዳር 11/2018 ዓ.ም ከቀኑ በ8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ከጨረታ መዝጊያ ቀንና ሰዓት በኋላ የሚቀርቡ የመጫረቻ ሰነዶች ተቀባይነት የላቸውም፡፡
- ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ጨረታውን በተመለከተ የተሻለ አማራጭ ካገኝ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- ሃያ ሁለት መክሊት ሕንፃ 10ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 10-01
ተጨማሪ ማብራሪያ ቢያስፈልግዎ በስልክ ቁጥር፡- 0116672342 ማነጋገር ይችላሉ።
የአዲስ አበባ ከተማ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለሥልጣን
