የድሬዳዋ ሁሉ አቀፍ ማማረፊያ ቤት ለ2018 የበጀት ዓመት ለሕግ ታራሚዎች ምግብ እህል፣ ጥራጥሬና ማጣፈጫዎች፣ ለስልጠና (ለብረታ ብረት እና እንጨት ሥራ) እና ጥገና ዕቃዎች፣ ለጽሕፈት መሣሪያዎች፣ ለፅዳት እና ለከፊል ቋሚ ዕቃዎች፣ ለኤሌክትሪክ ሥልጠናና ጥገና፣ ለመ/ልማት ግንባታ የሚውሉ ዕቃዎች ግብዓቶች/ እና ለውበትና ፀጉር ሥራ ቅባቶችና ዕቃዎች፣ ለልብስ ስፌት ሥራ ስልጠናና ለደንብ ልብስ አገልግሎት የሚውሉ ጨርቃ ጨርቅና ልዩ ልዩ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የድሬዳዋ ሁሉ አቀፍ ማማረፊያ ቤት ለ2018 የበጀት ዓመት ለሕግ ታራሚዎች ምግብ እህል፣ ጥራጥሬና ማጣፈጫዎች፣ ለስልጠና (ለብረታ ብረት እና እንጨት ሥራ) እና ጥገና ዕቃዎች፣ ለጽሕፈት መሣሪያዎች፣ ለፅዳት እና ለከፊል ቋሚ ዕቃዎች፣ ለኤሌክትሪክ ሥልጠናና ጥገና፣ ለመ/ልማት ግንባታ የሚውሉ ዕቃዎች ግብዓቶች/ እና ለውበትና ፀጉር ሥራ ቅባቶችና ዕቃዎች፣ ለልብስ ስፌት ሥራ ስልጠናና ለደንብ ልብስ አገልግሎት የሚውሉ ጨርቃ ጨርቅና ልዩ ልዩ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚሁ መሰረት በጨረታ ላይ ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች፡-
ከላይ የተገለፁትን ልዩ ልዩ ዕቃዎችን በሚወዳደሩበት ዘርፍ የተሰማሩትን በዘመኑ የታደሰ ሕጋዊ የንግድ ሥራ ፈቃድ፣ የሚፈለግባቸውን የመንግሥት ግብር አጠናቀው የከፈሉ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ መደረጉን የሚያረጋግጡ መረጃዎች፣ የዕቃ (የአገልግሎት) አቅራቢዎች ምዝገባ ስለመታቀፋቸው ከንግድ ሚኒስቴር የተሰጣቸውን የምዝገባ ምስክር ወረቀት ወይም ከግዥ ኤጀንሲ በተለቀቀ የመረጃ መረብ ውስጥ ተመዝግበው የሚገኙ እንዲሁም የሀገር ውስጥ ገቢ ባለሥልጣን 2018 ዓ.ም ጨረታ ላይ ለመሳተፍ የሚያስችል የምስክር ወረቀት እና ሌሎች ሕጋዊ ማስረጃዎችን ለዚሁ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ በታሸገ ፖስታ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ እንዲሁም ተጫራቾች የሚጫረቱበትን የጨረታ ዓይነት የቴክኒክና የዋጋው ሰነድ በአንድ ኤንቨሎፕ በማድረግና በማሸግ በግልጽ በፖስታው ላይ በመፃፍና በመፈረም ለዚሁ ጨረታ ተብሎ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ በታሸገ ፖስታ ማስገባት አለባቸው።
- ተጫራቾችም ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 (አስር) ቀን በአየር ላይ የሚቆይ ሲሆን፣ በአማርኛ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ዘወትር በሥራ ቀንና ሰዓት በድሬዳዋ ማ/ቤት ግዢ ቡድን ቢሮ ቁጥር 311 በመቅረብ የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር ብቻ) በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ከባንክ በተረጋገጠ CPO ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና መጠን፣ ጨረታው የሚዘጋበት እና የሚከፈትበት ቀንና ሰዓት በተመለከተ እንዲሁም ሌሎች ዝርዝር መረጃዎችን በጨረታ ሰነድ ውስጥ ያገኙታል፡፡
- ተጫራቾች ሰነዶችን ለማስገባት ሲመጡ ለሚጨረቱባቸው የዕቃዎች ናሙና አብረው ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው ቢገኙም ባይገኙም የቴክኒካልና የፋይናንሺያል የጨረታ ሰነዱ በመ/ቤታችን አዳራሽ በተባለው ቀንና ሰዓት ተዘግተው ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
ተጨማሪ መረጃ ቢያስፈልገዎት ስልክ፡-
02 54 11 66 ወይም 02 51 11 28 64 ይደውሉ።
በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን የድሬዳዋ ሁሉ አቀፍ ማረሚያና ማረፊያ ቤት
