በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት በሰሜን ሸዋ ዞን ኤ/ግ/ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት የግዥ ንብ/አስ/ቡድን በ2018 በጀት አመት የተለያዩ ያገለገሉ እና ያላገለገሉ በወረዳችን ሥር ባሉ ሴክተር ፅ/ቤቶች የግብርና መገልገያ መሳሪያዎችን ብረታ ብረት፣ የተለያዩ ፕላስቲክ ጎማዎች እና የመኪና ጎማ፣ የተሰባበሩ ሸልፎች፣ወንበሮችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ኤግገ/09/156/2018
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት በሰሜን ሸዋ ዞን ኤ/ግ/ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት የግዥ ንብ/አስ/ቡድን በ2018 በጀት አመት የተለያዩ ያገለገሉ እና ያላገለገሉ በወረዳችን ሥር ባሉ ሴክተር ፅ/ቤቶች የግብርና መገልገያ መሳሪያዎችን ብረታ ብረት፣ የተለያዩ ፕላስቲክ ጎማዎች እና የመኪና ጎማ፣ የተሰባበሩ ሸልፎች፣ ወንበሮችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
በዚህም መሠረት መግዛት የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ምድብ/ሎት መሠረት እንድትሳተፉ ይጋብዛል፡፡
- ሎት አንድ የግብርና መገልገያ መሳሪያዎች እና ብረታ ብረቶች
- ሎት ሁለት የተለያዩ የፕላስቲክ ጎማዎች እና የመኪና ጎማ
- ሎት ሦስት የተሰባበሩ ሸልፎች እና ወንበሮች
- ተጫራቾች ስለጨረታ ዝርዝር ሁኔታ የሚገልፅ የጨረታ ሠነዶችን ለእያንዳንዱ ምድብ/ሎት የማይመለስ 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል በኤ/ግ/ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ፋይናንስ ቡድን ቢሮ ቁጥር 4 ገንዘቡን በመክፈል የጨረታ ሠነዱን በግዥ ንብ/አስ ቡድን ቢሮ ቁጥር 6 መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
- የእቃዎቹን አይነት እና ዝርዝር ሁኔታ ለማየት ከፈለጉ ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 2:30-11:30 በኤ/ግ/ወረዳ ግብርና ፑል፣ጤና እና አስተዳር ፑል ንብረት ክፍል በመገኘት ማየት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለእያንዳንዱ ሎት የጨረታ ማስከበሪያ ለሎት አንድ የግብርና መገልገያ መሳሪያዎች፣ ብረታ ብረቶች 20,000 (ሀያ ሺህ ብር)፣ ሎት ሁለት የተለያዩ የፕላስቲክ ጎማዎች እና የመኪና ጎማ 2,000 (ሁለት ሺህ ብር)፣ ሎት ሦስት የተሰባበሩ ሸልፎች እና ወንበሮች 1000 (አንድ ሺህ ብር) በጥሬ ገንዘብ ገቢ ደረሰኝ ወይም በታወቁ ባንኮች ሲፒኦ በማሲያዝ ከጨረታ ሠነዱ ጋር ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- ተጫራቾች የሚሰጡትን የጨረታ ዋጋ የጨረታ ሠነዱ በሚጠይቀው መሠረት በሙሙላት ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከ28/02/2018 እስከ 12/03/2018 ለተከታታይ ለ15 ቀናት በአየር ላይ የሚቆይ ሆኖ በ16ኛው ቀን 13/03/2018 ከጠዋቱ 3፡30 ሰዓት ታሽጐ 4፡00 ሰዓት ቢሮ ቁጥር 6 ይከፈታል፣
- ተጫራቾች ጨረታው በሚከፈትበት ቀን እና ሰዓት መገኘት የጨረታውን ሂደት ሙሉ በሙሉ የመከታተል መብታቸው የተጠበቀ ነው ተጫራቾች ባይገኙም ጨረታው የሚከፈት ይሆናል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መበቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ታሽጎ የሚከፈት ይሆናል፡፡
- በጨረታው አሸናፊ የሚሆነው ተጫራች በሎት በጥቅል ዋጋ ከፍተኛ የሞላ ሲሆን በሎቱ የተጠቀሱትን እቃዎች ሙሉ በሙሉ ዋጋ መሙላት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች በጨረታው አሸናፊ ከሆኑ በኋላ የሚሸጠው እቃ መጠን ከታወቀ በኋላ በአሸነፉበት በኪሎ፣በቁጥር እና በሜትር ዋጋ ስሌት ጠቅላላ ብር ወረዳው ገንዘብ ፅ/ቤት ሂሳብ ቁጥር ገቢ በማድረግ የአሸነፉትን እቃ ከ10-15 ባሉት ተከታታይ ቀናት ውስጥ ማንሳት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች በሁሉም ሎቶች ላይ መወዳደር ይችላሉ።
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግሥት በሰሜን ሸዋ ዞን ኤ/ግ/ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
