በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል/መ/ቴ/ት/ሥ/ቢሮ የሺንሸቶ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ 2018 ዓ.ም በጀት ዘመን የሥልጠናና አላቂ ዕቃዎችንና የተለያዩ ቋሚ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ 01/2018
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል/መ/ቴ/ት/ሥ/ቢሮ የሺንሸቶ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ 2018 ዓ.ም በጀት ዘመን የሥልጠናና አላቂ ዕቃዎችንና የተለያዩ ቋሚ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
- ሎት 1፡- ኤሌክትሪክ እንስታሌሽን
- ሎት 2፡- ብረታ ብረት/ GEFA
- ሎት 3፡- ማሶኖሪ ግንባታ
- ሎት 4፡- ሳኒተሪ
- ሎት 5፡- አ.ይ.ት /ICT/
- ሎት 6፡- ደንብ ልብስ
- ሎት 7፡- የቤት ዕቃዎች
- ሎት 8፡- አላቂና ሌሎች አላቂ ጽ/መሳሪያዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
በዚህ መሰረት በዘርፉ ህጋዊ ፈቃድ ያላቸው፣የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ የዕቃ አቅራቢነት ሰርተፊኬት ያላቸውና የቫት ተመዝጋብ የሆኑ ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ተከታታይ 4 ቀን አየር ላይ ከዋለ በኋላ ማለትም ከ5ኛው የሥራ ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 10 ቀናት ዘወትር ሥራ ሠዓት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ከምባታ ዞን በሚገኘው የሺንሽቶ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ በመምጣት የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ ብር 300 (ሶስት መቶ ብር) ለእያንዳንዱ ሰነድ እየከለፈላችሁ መግዛት የምትችሉ ሲሆን ተጫራቾች የምግዙበትን ዋጋ ባቀረቡበት ሰነድ ላይ ዋጋ ማቅረቢያ ቦታ በመሙላት የጨረታ ማስከበሪያ ለእያንዳንዱ ሰነድ 5,000 (አምስት ሺህ ብር) ብቻ በCPO ወይም በባንክ የተመሰከረለት ቼክ፣ በጥሬ ገንዘብ በማስያዝ ሰነዱን ኮሪጅናልና አንድ ኮፒ በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግና የሚቀርበው ዋጋ ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ለ60 የሥራ ቀናት ፀንቶ የሚቆይ ሲሆን ሰነዱን ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ከምባታ ዞን በሚገኘው የሺንሸቶ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያ ኮሌጅ ግቢ ውስጥ እየመጣችሁ በመግዛትና በ11ኛው ቀን ማስገባት የሚትችሉ ሲሆን ይህ ቀን ቅዳሜ፣ እሁድ ወይም ህዝባዊ በዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በ4፡00 ሠዓት የጨረታ ሳጥን ታሽጎ በዚያው ከቀኑ 4፡30 ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ጨረታውን ተወዳድሮ ካሸነፉ ውል በመግባት ጥረቱንና ደረጃውን የጠበቀ ዕቃዎችን ወደ ሺንሽቾ ኮንስትራከሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ ድረስ በማምጣት ማስረከብ ይጠበቅባቸዋል።
ማሳሰቢያ፡- ኮሌጁ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ሆነ በከፍል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥር 046 339 0681/ 09 23 76 79 87/ 09 10 46 19 26/ 09 16 60 50 42
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል/መ/ቴ/ት/ሥ/ቢሮ የሺንሽቾ ኮንስትራክሽንና ኢንዱስትሪያል ኮሌጅ
